Friday, December 18, 2015
ትግላችንን ተጠናክሮ በአንድነት ይቀጥል!
December 17, 2015
የኦሮሞ ህዝብ መብቴ ይከበርልኝ ብሎ መነሳቱን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ከያቅጣጫው ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው። ይህ ለነጻነት ሃይሎች ብስራት ሲሆን ዘርን ከዘር በማጋጨት የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ለሚፈልገው የሽፍታ አገዛዝ ደግሞ ትልቅ መርዶ ነው። ባለፉት 25 ዓመታት ወያኔ አንዱን ዘር ከሌላው ዘር እያጋጨ፣ በወንድማማቾችና እህትማማቾች መካከል መተማመን እንዳይፈጥር መርዙን ሲረጭ ቆይቷል፤ ያሰበው አልሰምርለት ሲል ደግሞ በአገሪቱ አንጡራ ሃብት በሸመተው ጠመንጃ ለመብቱ የተነሳውን ህዝብ ደረት ደረቱን እየመታ ፈጅቶታል። በተለይም የአማራው ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድነት ተሰልፎ በህወሃት አገዛዝ ላይ የነጻነት ክንዱን ለማሳረፍ እንዳይችል ሌት ተቀን የጥላቻ መርዙን በመርጨት ከሌላው ህዝብ ጋር እንዲጋጭ ለማድረግ በእጅጉ ደክሟል። ወያኔ የረጨውን የጥላቻ መርዝ የኦሮሞ እና የአማራ ልጆች በጋራ እያረከሱት መገኘታቸው፣ የሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦች ህዝቦችም እንዲሁ ” አንለያይም” በማለት በጋራ ለመሰለፍና ትግሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነታቸውን መግለጻቸውና በተግባር እያሳዩ መምጣታቸው የ25 አመታት የወያኔ የአፈናና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ እያከተመ መምጣቱን የሚያመላክት ነው። ወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው በመላው ኢትዮጵያውያን ትብብር እንደረከሰበት ሲያውቅ ደግሞ የግድያ አዋጅ አውጥቶ በ-ኢትዮጵያውያኑ ላይ ጥይት አርከፍክፎ ጸጥ ሊያሰኛው መዘጋጀቱን በአዋጅ አስነግሯል። ከታሪክ መማር የማይችለው ጠባቡ ወያኔ፣ ህዝባቸውን አዋጅ አስነግረው የገደሉ ጨቋኝ መንግስታት መጨረሻቸው ምን እንደነበረ እንኳን ቆም ብሎ ማሰብ አልቻለም። ዛሬ የእሳት ላንቃ በሚተፋ ጠመንጃቸው ሊጨፈልቀው የሚያስበው ህዝብ ነገ መልሶ ራሱን እንደሚጨፈልቀው ለአፍታም ቢሆን ለማሰላሰል አልቻለም። የዘረፈው ሃብትና የታጠቀው መሳሪያ አእምሮውን ደፍኖት፣ እየመጣ ያለውን ህዝባዊ ሱናሚ ለማየት ተስኖታል። በጦር መሳሪያ ጋጋታና ድንፋታ ቢሆን ኖሮ ወራሪዋ ጣሊያን እስከዛሬ ድረስ ከአገራችን ለቃ ባልወጣች ነበር፣ በጦር መሳሪያ ጋጋታ ቢሆን ኖሮ እነ ጋዳፊን ዛሬ ቤተመንግስት እንጅ መቃብር ውስጥ አናገኛቸውም ነበር።
የአገራችን ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለነጻነቱ የሚያደርገውን ትግል በጥንቃቄ የሚመራበት ጊዜ ላይ ነን ። የገጠመን ጠላት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ፣ የገዛ ህዝቡን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋው የተነሳ በመሆኑ፣ አገዛዙ እስከዛሬ ካደረሰው ጥፋት ሌላ ተጨማሪ ጥፋት ሳያጠፋ፣ ከአገራችን መሬት ለመንቀል እንድንችል እርምጃችን ሁሉ ጥንቃቄ የተሞላበት ሊሆን ይገባል። ጠላታችን ህዝብን ከህዝብ ለማፋጀት ያለ የሌለ ሃይሉን የሚጠቀም መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ሁሉ ህዝቡን በጅምላ ለመፍጀት ወደ ሁዋላ የማይል ነው። ህዝቡ የጠላቱን አውሬነት ተገንዝቦ እሱ በሚከፍተው ቀዳዳ ዘው ብሎ ላለመግባት መጠንቀቅ አለበት። ሊገድሉን ሲመጡ ዘወር ብሎ በማሳለፍ፣ እንደገና ደግሞ ወደ አደባባይ በመውጣት፣ እንዲሁም የተቃውሞውን አድማስ በማስፋትና የሃይል መከፋፈል እንዲፈጠር በማድረግ ወያኔን አዳክሞና ተስፋ አስቆርጦ ካለሙት ግብ መድረስ ይቻላል። አሁን እየታየ ያለው አንድነት ይበልጥ እየተጠናከረ፣ ከኦሮሞው ጎን አማራው፣ ከአማራው ጎን ጉራጌው፣ ከጉራጌው ጎን ትግሬው፣ ከትግሬው ጎን አፋሩ፣ ከአፋሩ ጎን ጋምቤላው፣ ከጋምቤላው ጎን ሀረሪው፣ ከሃረሪው ጎን ጉሙዙ፣ ከጉሙዙ ጎን አዲስ አበቤው፣ ከአዲስ አበቤው ጎን ጋሞው በአጠቃላይ መላው ህዝብ እጅ ለእጅ እየተያያዘ የነጻነት ባበሩ ወደፊት እንዲሮጥ ማድረግ አለበት። ወጣቱ ራሱን ባለበት ቦታ እያደራጀና አመራር እየሰጠ በያቅጣጫው የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ ይቀጥል።
አርበኞች ግንቦት7 ትግሉን በተለያዩ አቅጣጫዎች አጠናክሮ ቀጥሎአል፤ የአርበኛው ሰራዊት የወያኔን ጀሌዎች በቀኝና በግራ መውጫና መግቢያ እያሳጣቸው ነው። የንቅናቄው አባላት በዳር አገር በአፈሙዝ፣ በመሃል አገር ደግሞ ወጣቱን እያደራጁ ለትግል እንዲሰልፍ እያደረጉት ነው። የንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ “ከነጻነት ትግሎች ጎን አለን” እንዳሉት የአርበኛው ልጆች ፊት ለፊት ተሰልፈው አመራር በመስጠት የነጻነት ትግሉን ለማቀጣጠል እና መከፈል ያለበትን የህይወት መስዋትነት ለመክፈል ተዘጋጅተው በያቅጣጫው እየተንቀሳቀሱ ነው።
ተደጋግሞ እንደተነገረው የአርበኞች ግንቦት7 አላማ በአገራችን የዲሞክራሲያዊ የሽግግር ስርዓት ማስጀመር ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ አላማ ዙሪያ ተሰልፎ ትግሉን ይቀጥል። ይህን አላማ የሚደግፉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ዛሬውኑ ከጎናችን ተሰልፈው ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው የሞት ሽረት ትግል ይሰለፉ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
አገራችን በልጆቿ ነጻ ትወጣለች!
አርበኞች ግንቦት7
አገራችን በልጆቿ ነጻ ትወጣለች!
አርበኞች ግንቦት7
Wednesday, December 16, 2015
ልብ በሉ፦
ልብ በሉ፦ ወያኔን ማስወገድ ያለብን የቅኝ ገዢዎች ተባባሪዎች፣ ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት፣ ክብርና ታሪክ
ፈጽሞ የማይጨነቁ፣ ሃገሪቱን ወደብ አልባ ያደረጉ፣ ኃይማኖትን የበከሉ፣ ሕዝቡን ለስደት ሞትዕና ለዳግም
ክፉ ቀን የዳረጉ ሰው መሰል ጨካኝ አራዊቶች ስለሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በኢንተርኔት፣ ፓልቶክ፣ ሬድዮና
ቴሌቪዥን በሚተላለፍ ትግልዕ ብቻ አይሞከርም። ዛሬ በአቶ መለስ የሙት መንፈስ ምስል እየተመራ
በመበታተኑ ጣዕረ ሞት የሚያቃስተውን ወያኔን ገፍትረን መጣል ካልቻልን ነገ አገግሞ ለሌላ መቅሰፍት
ይዳርገናል።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።
ፈጽሞ የማይጨነቁ፣ ሃገሪቱን ወደብ አልባ ያደረጉ፣ ኃይማኖትን የበከሉ፣ ሕዝቡን ለስደት ሞትዕና ለዳግም
ክፉ ቀን የዳረጉ ሰው መሰል ጨካኝ አራዊቶች ስለሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በኢንተርኔት፣ ፓልቶክ፣ ሬድዮና
ቴሌቪዥን በሚተላለፍ ትግልዕ ብቻ አይሞከርም። ዛሬ በአቶ መለስ የሙት መንፈስ ምስል እየተመራ
በመበታተኑ ጣዕረ ሞት የሚያቃስተውን ወያኔን ገፍትረን መጣል ካልቻልን ነገ አገግሞ ለሌላ መቅሰፍት
ይዳርገናል።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።
Saturday, December 12, 2015
Friday, December 11, 2015
Sunday, December 6, 2015
የአቶ መለስ ራዕይ 2
የአቶ መለስ ራዕይ 2
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።
Subscribe to:
Posts (Atom)

