Wednesday, October 26, 2016

ኢትዮጵያ ስትበታተን ምናምን ለምትሉ ሁሉ!
ኢትዮጵያ መቼም አትበታተንም የትግሉ ባለቤት ህዝቡ ስለሆነ የነጻነት ቻርተርም ሆነ ሌላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ራሱ የሚቀርጸው ነው የሚሆነው።የአርባ ዓመቱ የግራ ክንፉ የትግል ዘይቤና የደደቢቱ ማኒፌስቶ አጥፊና ትውልድን ገዳይ አንድነትን አጨናጋፊ ነው። እነዚህኑ የግራው ክንፍ ፖለቲካ በደርግ ዘመን ለአስራ ሰባት ዓመት በወያኔ ዘመን ለሃያ አምስት ዓመት ባጠቃላይ ለአርባ ዓመት በተግባር አይተን ፈትነናቸው እርባና ቢስነታቸውን ሙሉ በሙሉ አረጋግጠናል። ይህ ትውልድ፣ ሃገር ቤት መከራውን የሚያየው ትውልድና ከጎኑ ያልተለዩት መሪዎቹ ራሳቸው ወደፊት ኢትዮጵያ የምትመራበትን ሠነድ በህብረት ማዘጋጀት ይኖርባቸዋል። ዛሬ የአማራውና ኦሮሞውን ትግል ተቀናጅቶ የወያኔው ከፋፋይ ማኒፌስቶ መቀዳደዱ ሕዝቡ የደረሰበትን የንቃት ደረጃ ያሳያል። ፖለቲካ ብዙ እምቅ ኃይልና እንቅስቃሴ በመሆኗ ሕዝቡ የራሱን ኢትዮጵያዊ ሠነድ ማዘጋጀት ይችል ዘንድ ላገሪቱ የወደፊት ዕጣ፣ ሠላምና መረጋጋት፣ እድገትና እርምጃ ራዕይ የሌላቸው ምሁራን ወይንም ፖለቲካንና ተግባርን አዛምዶ ማየት የማይችሉ የግራው ትግል ዘይቤ የወለዳቸው ሰዎች ጣልቃ መግባቱን ትተው ይህን ሃገራዊ ኃላፊነት ለባለቤቱ ለሕዝቡ ቢተዉለት መልካም ነው።
አዲሱን ሠነድ የኢትዮጵያ ሕዝብና አብረውት መከራውን የቀመሱት መሪዎቹ ያዘጋጁ። ሠርጎ ገቦች፣ ገዳዮችና አሽቃባጮች ተዉ ሊባሉ ይገባል።

T&T's disscussion on Oromo charter, Oromo transitional government and Or...

የኦሮሚያን ቻርተርን በማዘጋጀት ላይ ነኝ ባለው ጁሀር መሀመድን የሞገተው ጋዜጠኛ ተስፋየ ተሰማ