Friday, January 22, 2016

ሕወሃት ስልጣን ከጨበጠ ጀምሮ በኢትዮጵያ የዘረጋዉ ፖለቲካ በዘር ላይ የተመሰረተ ከፋፋይ ፖለቲካ ነዉ። ኢትዮጵያ የብዙ ብሄረሰብ አገር ናት። በታሪኳ የተሰሩ ብዙ ስተቶችና በደሎች አሉ። በአንጻሩም ደግሞ ኢትዮጵያዉያን ከተለያዩ ቋንቋዎችና ክልሎች በሰላም በፍቅር ኖረዋል፣ ተዋደዋል፣ ተደባልቀዋል።ሆኖም ግን በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያዉያን በሃገር ዉስጥ እና በአለም ዙሪያ ባደረጉት ሰላላምዊ ስለፎች ለማየት እንደተቻለዉ አብሮ የመሥራቱንና በጋራ የመንቀሳቀሱን አማራጭ የወሰዱ ይመስላል። ይህ መልካ ጅማሬ የበለጠ ተጠናክሮ ከገፋ ያለምንም ጥያቄ የሕወሃት ፍጻሜ እንደሚሆን መጠራጠር የለብንም።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።