Sunday, December 6, 2015

የአቶ መለስ ራዕይ 2

የአቶ መለስ ራዕይ 2
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

No comments:

Post a Comment