የነብርን ጭራ አይዙ ከያዙ አይለቁ!
እነሆ እኛ ኢትዮጵያዉያን ህብረት፣ መደጋገፍ፣ ስምምነትና አርቆ አሳቢነት የሚጠይቅበት ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል። ያለፉት ዓመታት የወያኔውን ጥቁር ሥርዓት ምንነት አሳይቶናል። ይህንን ብቻ አይደለም፤ በአምባገነን ሥርዓትና ለቅኝ ገዥዎች በባንዳነት በሚያድር ሥርዓት መካከል ያለውን ልዩነትም በሚገባ አሳውቆናል። የንጉሡ ዘመን ኋላ ቀር ነበር። የደርግ ዘመን አምባገነን ነበር። በሁለቱም ሥርዓት ወቅት ግን ሃገር ነበረች። ኢትዮጵያ እስከ ባህረ በሯ ሉዓላዊ እስከ ሕዝቦቿ ክቡር ነበረች። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ወያኔ ዘረኛ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሙስናዊ አምባገነን ሥራዓት ቋሚ ተጠሪ ስብስብ ተቋም ብቻ አይደለም። ወያኔ "የአናቁረህ ግዛ" ግፍ አራማጅ ብቸኛ የቀማኞች ድርጅት ብቻ አይደለም። ወያኔ ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያን ለውጭ ባለሃብቶች የሸበሸበ የኃጢአተኞችና "የአስረሽ ምቺ" ዳንኪረኞች፣ መዝባሪዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሁሉም የኃጢዓት ሥርዓቶች ድምር ነው። ወያኔ ድንገት ከተሰባሰበበት ደደቢት ሸለቆ ተንከባሉ ሠይጣን ዋሻ ውስጥ ለአመታት ከርሞ ዲያቢሎስ ሳያኝክ የተፋው የርኩስ ሥርዓት ቁንጮ ነው። እድሏ ሆኖ ቅድስት ኢትዮጵያ የዚህ ሥርዓት ተሸካሚ ሆናለች። እንዲያ እንዳልተከበረች፣ እንዲያ እንዳልተፈራች ሃገራችን ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ቅርጫ ቀረበች። ሥርዓቱ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ኢትዮጵያን በቁሟ የገነዘ፣ ሕዝቧን ያስጨነቀ መሪር ሥርዓት ነው። ኢትዮጵያ ሃገራችንን ከዚህ ሥርዓት የሚገላግላት ቆራጥነትና በህብረት መነሳት ብቻ ነው። ህዝብን በመርዘኛ ራዕይ ሰልቦ፣ ወጣቱን በሥራ አጥነት አጠውልጎ ለስደትና ሴተኛ አዳሪነት እየዳረገ፣ ነዋሪውን በልማት ስምና በከተማ ማስፋፋት እያፈናቀለ ሕዝብን በቅኝ ገዥዎች ቋንቋና በምጣኔ ኃብት እድገት እያደናገረ የሃገሪቱን ሃብት መዝብሮ ወደ ውጭ በማሸሽና በከፍተኛ ዕዳ ውስጥ በመዝፈቅ በጥቂቶች ስም ሃብት እያከማቸ እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊገዛ የሚቃጣ ዘመነኛ የግፍ ሥርዓት አራማጅ ወያኔ ብቻ ነው።
በዘረፉት ገንዘብ ልጆቻቸውን እንደ ልዑላውያን ልጆች በምዕራቡ ዓለም ወይም ቻይና በቅምጥል ሊያኖሩ የሚያስቡ ሞኞች ወቅቱን ያልተገነዘቡ ብቻ ናቸው። ከጭቁን ሕዝብ በተመዘበረ ነዋይ ኬክ ገዝቶ መዘመር፣ ሻምፓኝ አንስቶ ጤንነትን መመኘት ሲዖል አፋፍ ቆሞ ዲያቢሎስን መጋበዝ መሆኑን እንዲሆም ከረሃብተኞች በተነጠቀ ገንዘብ በተገዛ ሸማ መዋብ በደም በተለወሰ ክር የተሰፋ መሆኑ ገና ያልገባቸው ይልቁንም የሥርዓቱ መበስበስ ገና ያልታያቸው ርህራሄ ቢሶች ብቻ ናቸው። ከድሆች መሬት ነጥቆ በሙስና፣ በዘረፋ በተገነቡ ዘመናዊ ሕንፃ ውስጥ መኖር ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ መቀበር መሆኑ ገና ያልገባቸው እብሪተኞች ብቻ ናቸው። ከድሆች አፍ በተነጠቀ ገንዘብ ሠማይ ጠቀስ ፎቆቻቸውን ወደ ላይ አንጋጠው የሚመለከቱ የፀሃይ ብርሃን የማትጠልቅ የሚመስላቸው መሃይማን ብቻ ናቸው። ግንዛቤ ያጠራቸው ባለስልጣናትና ልጆቻቸው የሙስናው ተጠቃሚዎች፣ ገና በሼራተንና ሂልተን አልኮል የሚራጩት፣ የሉካንዳው ቤት ሠልፈኞች፣ የዳንኪራ ቤቱ ጋጠ ወጦችም ጭምር ሕዝባዊው ሱናሜ መምጣቱን ፈፅሞ ያልተገነዘቡት ዘመኖች ናቸው። እነርሱ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደሚፈነጥዙ ዓይነት የግፍ ሥሪቶች ናቸውና የገናናዋ ኢትዮጵያ እንባ ያቅበዘብዛቸዋል። የገባቸው፣ አዎ የገባቸው ገዥዎች፣ ነገ ዓይደለም ዛሬውኑ ራሳቸውን ነፃ ያወጣሉ። የገባቸው፣ የአምላክ ምህረት የቀረባቸው፣ ይቅርታ ጠይቀው መጪው ዘመን ለነሱም ለሃገሪቱም ብሩህ እንዲሆን ይተጋሉ። የገባቸው፣ ልባቸው ያልደነደነው የግፍ ሥርዓት ፈጽሞ እንዲቀበር የሚመኙ የሕዝቡን ጥያቄ ይቀበላሉ። የገባቸው፣ የድሆች እንባ ሲንቆረቆር አይተው ልባቸው በርኅራሄ የረሰረሰው አዲስ ታሪክ ይሠራሉ። ያዘኑ፣ የረሃብተኛውን ሕጻን አጥንት የቆጠሩ የነጠፉ ጡቶችን አይተው የሚያለቅሱ ገዥዎች ሥልጣናቸውን በሠላም ለህዝብ ያስረክባሉ። ዕድሉ አሁንም አለ። ይህ ዕድል ነገ ላይኖር ይችላል። ሳዳም ሁሴንና ጋዳፊ፣ ያውም ሃገራቸውን ከልብ የሚወዱት እንኳን ይህ ዕድል አምልጧቸዋል። እናንተስ?
ዛሬ የበደሉ ጽዋ ሞልቶ ቢፈስ ሕዝብ በቁጣ ተነስቷል። ሕዝብ በቃኝ፣ መረረኝ ብሏል። ሁሉም ሊተባበርና ከትግሉ ጎን መሰለፍ አለበት። ዛሬ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ጉራጌ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ወላይታ፣ ሲዳማ፣ አኙዋክ፣ ከንባታ፣ ከፊቾ እያልን የገበጣ ጨዋታ የምንጫወትበት ወቅት አይደለም። እኛ ኢትዮጵያውያን እንደቀድሞ ተታለን አንድ የበሰበሰሰ ሥርዓት በሌላ አፋኝ ሥርዓት ሲተካ አይተን ዝም የምንል ወይንም ወያኔ አንዱን ዘር ካንዱ ሊያጋጭ በተለመው "የአልሞት ባይ ተጋዳይ" ስልቱ ውስጥ የምንዘፈቅለት ቂሎች አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያውያን ትግሉን አመካኝቶ ሌላ ነውጥ ሊያመጣ የሚችል ኃይልን እሹሩሩ የምንልም አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ በኋላ ፈጽሞ አንከፋፈልም። የወያኔው ሥርዓት የጥቁር አምባገነንነትን ቀለም፣ የአንድ ዘር የበላይነት የቅኝ ገዥዎች ቅጅ የግፍ አገዛዝ መርህን፣ የእብለት አካሄድንና የሸፍጥ ስልት ፖለቲካ ምንነትን እንድናውቅ አስችሎናል። በእርግጥ ዘረኝነትንና ልዩነትን አሽቀንጥረን በኅብረት እንድንታገል፣ በአንድ ላይ እንድንቆምም ትምህርት ሆኖናል። በልማት ስም ቅኝ አገዛዝዝን በዲሞክራሲ ስም ጭለማ ያመጣብንን ሥርዓት ሁላችንም መርምረነዋል። እነሆ ዛሬ - ሁላችንም በአንድነት "መሬት ላራሹና" "ሕዝባዊ መንግሥት" ይመስረት መፈክሮችን የምንተገብርበት ወሳኝ ዘመን ላይ ደረስናል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከዳር እስከ ዳር በአንድነት ተነስቷል። ዛሬ የተጀመረው ሕዝባዊ ትግል ቢዳከም እንደገና መቀመቅ ውስጥ የምንገባው እኛው ነንና ትግሉን ይበልጥ ማፋፋም አለብን። "የነብርን ጭራ አይዙ - ከያዙ አይለቁ!
ሕዝብ ያሸንፋል፤ ኢትዮጵያ እንደቀድሞዋ በነጻነትዋ ትራመዳለች። ኢትዮጵያ ግርማ ሞገሥዋ ይመለሳል።
ሚክያስ ግዛው
እነሆ እኛ ኢትዮጵያዉያን ህብረት፣ መደጋገፍ፣ ስምምነትና አርቆ አሳቢነት የሚጠይቅበት ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል። ያለፉት ዓመታት የወያኔውን ጥቁር ሥርዓት ምንነት አሳይቶናል። ይህንን ብቻ አይደለም፤ በአምባገነን ሥርዓትና ለቅኝ ገዥዎች በባንዳነት በሚያድር ሥርዓት መካከል ያለውን ልዩነትም በሚገባ አሳውቆናል። የንጉሡ ዘመን ኋላ ቀር ነበር። የደርግ ዘመን አምባገነን ነበር። በሁለቱም ሥርዓት ወቅት ግን ሃገር ነበረች። ኢትዮጵያ እስከ ባህረ በሯ ሉዓላዊ እስከ ሕዝቦቿ ክቡር ነበረች። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ወያኔ ዘረኛ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሙስናዊ አምባገነን ሥራዓት ቋሚ ተጠሪ ስብስብ ተቋም ብቻ አይደለም። ወያኔ "የአናቁረህ ግዛ" ግፍ አራማጅ ብቸኛ የቀማኞች ድርጅት ብቻ አይደለም። ወያኔ ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያን ለውጭ ባለሃብቶች የሸበሸበ የኃጢአተኞችና "የአስረሽ ምቺ" ዳንኪረኞች፣ መዝባሪዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሁሉም የኃጢዓት ሥርዓቶች ድምር ነው። ወያኔ ድንገት ከተሰባሰበበት ደደቢት ሸለቆ ተንከባሉ ሠይጣን ዋሻ ውስጥ ለአመታት ከርሞ ዲያቢሎስ ሳያኝክ የተፋው የርኩስ ሥርዓት ቁንጮ ነው። እድሏ ሆኖ ቅድስት ኢትዮጵያ የዚህ ሥርዓት ተሸካሚ ሆናለች። እንዲያ እንዳልተከበረች፣ እንዲያ እንዳልተፈራች ሃገራችን ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ቅርጫ ቀረበች። ሥርዓቱ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ኢትዮጵያን በቁሟ የገነዘ፣ ሕዝቧን ያስጨነቀ መሪር ሥርዓት ነው። ኢትዮጵያ ሃገራችንን ከዚህ ሥርዓት የሚገላግላት ቆራጥነትና በህብረት መነሳት ብቻ ነው። ህዝብን በመርዘኛ ራዕይ ሰልቦ፣ ወጣቱን በሥራ አጥነት አጠውልጎ ለስደትና ሴተኛ አዳሪነት እየዳረገ፣ ነዋሪውን በልማት ስምና በከተማ ማስፋፋት እያፈናቀለ ሕዝብን በቅኝ ገዥዎች ቋንቋና በምጣኔ ኃብት እድገት እያደናገረ የሃገሪቱን ሃብት መዝብሮ ወደ ውጭ በማሸሽና በከፍተኛ ዕዳ ውስጥ በመዝፈቅ በጥቂቶች ስም ሃብት እያከማቸ እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊገዛ የሚቃጣ ዘመነኛ የግፍ ሥርዓት አራማጅ ወያኔ ብቻ ነው።
በዘረፉት ገንዘብ ልጆቻቸውን እንደ ልዑላውያን ልጆች በምዕራቡ ዓለም ወይም ቻይና በቅምጥል ሊያኖሩ የሚያስቡ ሞኞች ወቅቱን ያልተገነዘቡ ብቻ ናቸው። ከጭቁን ሕዝብ በተመዘበረ ነዋይ ኬክ ገዝቶ መዘመር፣ ሻምፓኝ አንስቶ ጤንነትን መመኘት ሲዖል አፋፍ ቆሞ ዲያቢሎስን መጋበዝ መሆኑን እንዲሆም ከረሃብተኞች በተነጠቀ ገንዘብ በተገዛ ሸማ መዋብ በደም በተለወሰ ክር የተሰፋ መሆኑ ገና ያልገባቸው ይልቁንም የሥርዓቱ መበስበስ ገና ያልታያቸው ርህራሄ ቢሶች ብቻ ናቸው። ከድሆች መሬት ነጥቆ በሙስና፣ በዘረፋ በተገነቡ ዘመናዊ ሕንፃ ውስጥ መኖር ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ መቀበር መሆኑ ገና ያልገባቸው እብሪተኞች ብቻ ናቸው። ከድሆች አፍ በተነጠቀ ገንዘብ ሠማይ ጠቀስ ፎቆቻቸውን ወደ ላይ አንጋጠው የሚመለከቱ የፀሃይ ብርሃን የማትጠልቅ የሚመስላቸው መሃይማን ብቻ ናቸው። ግንዛቤ ያጠራቸው ባለስልጣናትና ልጆቻቸው የሙስናው ተጠቃሚዎች፣ ገና በሼራተንና ሂልተን አልኮል የሚራጩት፣ የሉካንዳው ቤት ሠልፈኞች፣ የዳንኪራ ቤቱ ጋጠ ወጦችም ጭምር ሕዝባዊው ሱናሜ መምጣቱን ፈፅሞ ያልተገነዘቡት ዘመኖች ናቸው። እነርሱ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደሚፈነጥዙ ዓይነት የግፍ ሥሪቶች ናቸውና የገናናዋ ኢትዮጵያ እንባ ያቅበዘብዛቸዋል። የገባቸው፣ አዎ የገባቸው ገዥዎች፣ ነገ ዓይደለም ዛሬውኑ ራሳቸውን ነፃ ያወጣሉ። የገባቸው፣ የአምላክ ምህረት የቀረባቸው፣ ይቅርታ ጠይቀው መጪው ዘመን ለነሱም ለሃገሪቱም ብሩህ እንዲሆን ይተጋሉ። የገባቸው፣ ልባቸው ያልደነደነው የግፍ ሥርዓት ፈጽሞ እንዲቀበር የሚመኙ የሕዝቡን ጥያቄ ይቀበላሉ። የገባቸው፣ የድሆች እንባ ሲንቆረቆር አይተው ልባቸው በርኅራሄ የረሰረሰው አዲስ ታሪክ ይሠራሉ። ያዘኑ፣ የረሃብተኛውን ሕጻን አጥንት የቆጠሩ የነጠፉ ጡቶችን አይተው የሚያለቅሱ ገዥዎች ሥልጣናቸውን በሠላም ለህዝብ ያስረክባሉ። ዕድሉ አሁንም አለ። ይህ ዕድል ነገ ላይኖር ይችላል። ሳዳም ሁሴንና ጋዳፊ፣ ያውም ሃገራቸውን ከልብ የሚወዱት እንኳን ይህ ዕድል አምልጧቸዋል። እናንተስ?
ዛሬ የበደሉ ጽዋ ሞልቶ ቢፈስ ሕዝብ በቁጣ ተነስቷል። ሕዝብ በቃኝ፣ መረረኝ ብሏል። ሁሉም ሊተባበርና ከትግሉ ጎን መሰለፍ አለበት። ዛሬ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ጉራጌ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ወላይታ፣ ሲዳማ፣ አኙዋክ፣ ከንባታ፣ ከፊቾ እያልን የገበጣ ጨዋታ የምንጫወትበት ወቅት አይደለም። እኛ ኢትዮጵያውያን እንደቀድሞ ተታለን አንድ የበሰበሰሰ ሥርዓት በሌላ አፋኝ ሥርዓት ሲተካ አይተን ዝም የምንል ወይንም ወያኔ አንዱን ዘር ካንዱ ሊያጋጭ በተለመው "የአልሞት ባይ ተጋዳይ" ስልቱ ውስጥ የምንዘፈቅለት ቂሎች አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያውያን ትግሉን አመካኝቶ ሌላ ነውጥ ሊያመጣ የሚችል ኃይልን እሹሩሩ የምንልም አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ በኋላ ፈጽሞ አንከፋፈልም። የወያኔው ሥርዓት የጥቁር አምባገነንነትን ቀለም፣ የአንድ ዘር የበላይነት የቅኝ ገዥዎች ቅጅ የግፍ አገዛዝ መርህን፣ የእብለት አካሄድንና የሸፍጥ ስልት ፖለቲካ ምንነትን እንድናውቅ አስችሎናል። በእርግጥ ዘረኝነትንና ልዩነትን አሽቀንጥረን በኅብረት እንድንታገል፣ በአንድ ላይ እንድንቆምም ትምህርት ሆኖናል። በልማት ስም ቅኝ አገዛዝዝን በዲሞክራሲ ስም ጭለማ ያመጣብንን ሥርዓት ሁላችንም መርምረነዋል። እነሆ ዛሬ - ሁላችንም በአንድነት "መሬት ላራሹና" "ሕዝባዊ መንግሥት" ይመስረት መፈክሮችን የምንተገብርበት ወሳኝ ዘመን ላይ ደረስናል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከዳር እስከ ዳር በአንድነት ተነስቷል። ዛሬ የተጀመረው ሕዝባዊ ትግል ቢዳከም እንደገና መቀመቅ ውስጥ የምንገባው እኛው ነንና ትግሉን ይበልጥ ማፋፋም አለብን። "የነብርን ጭራ አይዙ - ከያዙ አይለቁ!
ሕዝብ ያሸንፋል፤ ኢትዮጵያ እንደቀድሞዋ በነጻነትዋ ትራመዳለች። ኢትዮጵያ ግርማ ሞገሥዋ ይመለሳል።
ሚክያስ ግዛው