ሕወሓት እና የመሬት ቅርምቱ
መሬት (Land)፣ መሬት በሕዝባዊ መንግሥት ቁጥጥር ሥር ስትውል ልማት ባግባቡ ይፋጠናል። በሃገራችን የመሬት ጉዳይ የፍትህ ጉዳይ አልፋና ኦሜጋ ነው። የተፈጥሮ ኃብት (Natural resources) ከጉልበትና ዓዕምሮ (labour and mental) ጋር ሲዋሃድ ምርትን (production) ያስገኛል። መሬት የተፈጥሮ ኃብት ዋነኛ መፍለቅያ ምንጭ ነች። ማንም ሠላምንና ጸጥታን፣ ልማትንና እድገትን የሚፈልግ ስብስብ የመሬትን ጉዳይ ፍትሃዊ (justify) ለማድረግ ሲል ጠቃሚ መሠረታዊ ህጎችን (system of rules)በቅጡ ይቀርጻል። ይህ ጉዳይ ፈጽሞ ተግባራዊ መሆን ካልቻለ ጥቁር ገበያዎች (black markets) እንደ አሸን ይፈላሉ። ጥቁር ገበያ በሙስና (Corruption) የሚመራ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ፍዳና ዕዳ ነው። መሬት የመንግሥት ኃብት እንዲሆን ፈላስፎችና የምጣኔ ኃብታዊ ሊቆች እጅግ ሠፊ ሳይንሳዊ ትንታኔ ሠጥተዋል። "መሬት ላራሹ" በኢትዮጵያ ተራማጆች ዙርያ ዘወትር ሲነሳ የቆየ ታሪካዊ መፈክር ነበር። የተጨቋኖችና አጋሮቻቸው እምቅ አስተሳሰብ የወለደው ይህ ታሪካዊ መፈክር ተንቆ ይባስኑ የኢቶዮጽያ መሬት የቀማኞችና ሙሰኞች መገልገያ ሆኗል። በኢቶዮጽያ መሬት አሞሌ ጨው ተሸክሞ ለመጣ ሁሉ በቀላሉ እንደምትቸረቸር ኮማሪት ተንቃለች። መሬት "በሶስተኛ ደላሎች" ስም እንደዋዛ የምትለወጥ ጉቦኛ ባለሥልጣናትና መዝባሪው ነጋዴ የሚሻሟት አሳዳሪ የራቃት ባለቤት አልባ ሆናለች። መሬት በኢቶዮጽያ ምን ያልሆነችው አለ? አሜሪካ የተፈጠረችው በቀይ ሕንዶች ደም ላይ ነው። አሜሪካ የተገነባችው በአፍሪካውያን ባርያዎች ግፍና ሰቆቃ ነው። ይህን ግፍ የዲሞክራሲ ቋሚ ምሰሶ ወይም ዓምድ አይደለም። ገዥው መንግሥት ሰዎችን በፌደራል ፖሊስ ጥይት ካስገደለ በኋላ "ለዲሞክራሲው ግንባታ ገና ነን፤ አሜሪካ እስከ ስድሳዎቹ መባቻ ድረስ ሰዎች ይገደሉ ነበር" ብሎ ያወራል። አገዛዙ ልማቱን እየዘረፈ፣ ሰዎችን እንደ ቀይ ሕንዶች ከቀዪአቸው እያፈናቀለ፣ ጥሬ ሃብቱን ለባዕድ እየቸረቸረና "መሬቴን አትንኩ" ያሉትን ነዋሪዎች እያሽመደመደ "ዲሞክራሲው ገና አልጎለበትም" ብሎ ያሾፋል። ይህን ትምህርት የቀሰሙት ከሱዛብን ራይስ ከሆነ ያሳዝናል። መልካሞቹን የዲሞክራሲ እሴቶችና የመልካም አስተዳደር መርህን ካደጉት ሃገሮች ተሞክሮ እየቀሰሙ ማዳበር ሲቻል መሬትን ለመቀራመት ብሎ ተወላጁን፣ አገር በቀሉን (indigenous) መግደል የዲሞክራሲ ባህሉም ወጉም አይደለም።



መሬት (Land)፣ መሬት በሕዝባዊ መንግሥት ቁጥጥር ሥር ስትውል ልማት ባግባቡ ይፋጠናል። በሃገራችን የመሬት ጉዳይ የፍትህ ጉዳይ አልፋና ኦሜጋ ነው። የተፈጥሮ ኃብት (Natural resources) ከጉልበትና ዓዕምሮ (labour and mental) ጋር ሲዋሃድ ምርትን (production) ያስገኛል። መሬት የተፈጥሮ ኃብት ዋነኛ መፍለቅያ ምንጭ ነች። ማንም ሠላምንና ጸጥታን፣ ልማትንና እድገትን የሚፈልግ ስብስብ የመሬትን ጉዳይ ፍትሃዊ (justify) ለማድረግ ሲል ጠቃሚ መሠረታዊ ህጎችን (system of rules)በቅጡ ይቀርጻል። ይህ ጉዳይ ፈጽሞ ተግባራዊ መሆን ካልቻለ ጥቁር ገበያዎች (black markets) እንደ አሸን ይፈላሉ። ጥቁር ገበያ በሙስና (Corruption) የሚመራ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ፍዳና ዕዳ ነው። መሬት የመንግሥት ኃብት እንዲሆን ፈላስፎችና የምጣኔ ኃብታዊ ሊቆች እጅግ ሠፊ ሳይንሳዊ ትንታኔ ሠጥተዋል። "መሬት ላራሹ" በኢትዮጵያ ተራማጆች ዙርያ ዘወትር ሲነሳ የቆየ ታሪካዊ መፈክር ነበር። የተጨቋኖችና አጋሮቻቸው እምቅ አስተሳሰብ የወለደው ይህ ታሪካዊ መፈክር ተንቆ ይባስኑ የኢቶዮጽያ መሬት የቀማኞችና ሙሰኞች መገልገያ ሆኗል። በኢቶዮጽያ መሬት አሞሌ ጨው ተሸክሞ ለመጣ ሁሉ በቀላሉ እንደምትቸረቸር ኮማሪት ተንቃለች። መሬት "በሶስተኛ ደላሎች" ስም እንደዋዛ የምትለወጥ ጉቦኛ ባለሥልጣናትና መዝባሪው ነጋዴ የሚሻሟት አሳዳሪ የራቃት ባለቤት አልባ ሆናለች። መሬት በኢቶዮጽያ ምን ያልሆነችው አለ? አሜሪካ የተፈጠረችው በቀይ ሕንዶች ደም ላይ ነው። አሜሪካ የተገነባችው በአፍሪካውያን ባርያዎች ግፍና ሰቆቃ ነው። ይህን ግፍ የዲሞክራሲ ቋሚ ምሰሶ ወይም ዓምድ አይደለም። ገዥው መንግሥት ሰዎችን በፌደራል ፖሊስ ጥይት ካስገደለ በኋላ "ለዲሞክራሲው ግንባታ ገና ነን፤ አሜሪካ እስከ ስድሳዎቹ መባቻ ድረስ ሰዎች ይገደሉ ነበር" ብሎ ያወራል። አገዛዙ ልማቱን እየዘረፈ፣ ሰዎችን እንደ ቀይ ሕንዶች ከቀዪአቸው እያፈናቀለ፣ ጥሬ ሃብቱን ለባዕድ እየቸረቸረና "መሬቴን አትንኩ" ያሉትን ነዋሪዎች እያሽመደመደ "ዲሞክራሲው ገና አልጎለበትም" ብሎ ያሾፋል። ይህን ትምህርት የቀሰሙት ከሱዛብን ራይስ ከሆነ ያሳዝናል። መልካሞቹን የዲሞክራሲ እሴቶችና የመልካም አስተዳደር መርህን ካደጉት ሃገሮች ተሞክሮ እየቀሰሙ ማዳበር ሲቻል መሬትን ለመቀራመት ብሎ ተወላጁን፣ አገር በቀሉን (indigenous) መግደል የዲሞክራሲ ባህሉም ወጉም አይደለም።


