"ሕዝባው መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቅል" ወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ"
ሚክያስ ሙሉጌታ ከ ኖርዌ
ድሮ ከዘውዱ መገርሰስ በፊት አዲስ አበባ እንደህ እንዳሁኑ ጭንቅንቅ ያላለች ለመሆኗ ትላልቆች ሲናገሩ እሰማለሁኝ። ብዙ
ሰዎች እርስ በእርሳችን እንተዋወቅ ነበር፣ ያለው ለሌለው ያዝናል፣ አውደ አመቱን በጋራ እናከብራለን ይላሉ። ቤት ገብቶ
የሚዘርፍ ሌባ ቀርቶ የተሰጣን ልብስ እንኳን ከውጭ አንስቶ የሚሰወር ወስላታ እምብዛም አይታይም ይላሉ። ሁሉም
በአቅሙ ሰርቶ ስለሚኖር የሰው እጅን መመልከት ነውር እንደነበርም ያወሳሉ። ሕዝቡ እግዚአብሄርን በጽኑ ያመልካል፣
በኢትዮጵያዊነቱ ይመካል፣ ባንዲራውን ይወዳል፣ ንጉሱንም ያከብራል፣ እያሉ ትላልቆቹ ዘወትር ሲያወሩ በጽሞና
አዳምጣለሁኝ።
እኔ የማውቃት አዲስ አበባ ግን ታላላቆቼ እንደሚያወሩላት አይደለችም። ምንድነው ምክንያቱ አልኳቸው? "ቀድሞ
ክርስትያኑና እስላሙ ተፋቅሮ የሚኖርባት፣ ባህልና ወጉ የሚናፍቁባት፣ ግብረገብነቱና ጨዋነቱ ጥልቅ የነበሩባት፣ የምሁሩ
እውቀትና የሕዝቡ ማስተውል እንደ እንቁ የሚብለጨለጩባት፣ ኪነቱ፣ ቴያትሩና ስነ ጥበቡ እውነትንና እምነትን
ሲያንጸባርቁባት የነበረችው አዲስ አበባ ዛሬ በክፋት ሠራዊትና በሙስና ባለሃብቶች በመወረሯ ነዋ" አሉኝ። በእርግጥ እኔም
እንደታዘብኩት የአዲስ አበባ መሬት ካቅሟ በላይ በስርቆት በተገነቡ ሕንፃዎች፣ በዳንኪራ ቤቶች፣ መሸታ ቤቶች፣ ቅባት
ቤቶች፣ የውበት ሳሎኖች፣ ላውንደሪዎች፣ መኪና አከራዮች፣ ወዘተ ተጨናንቃለች።
የኢጣልያ የቅኝ ገዢነት ሕልም ለማብከን መኳንንቱ የመከሩበት የእምዬ ሚኒልክና የነብር አራስዎ እቴጌ ጣይቱ መናኸርያ
ያ ታላቁ ቤተ መንግስት ኢትዮጵያን በማይወዱት ሰዎች ተይዟል። የንጉሠ ነገስቱ ኃይለሥላሴ ማደርያ ኢዮቤልዩ ቤተ
መንግስትም ተደፍሯል። ደርግ ታላላቆቹ የሀገር ኃብት የነበሩትን ወደር የለሽ ምርጥ ምሁራን ቢገድልም አብዛኛዎቹን ንጉሱ
ያስተማሯቸውን ብቁ ምሁራን ተጠቅሞባቸው ነበር። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ብቃቱ ፈጽሞ የሌላቸው የወያኔ የጫካ ሽፍቶች
የመንግስት መዋቅሩን ሲያዛንፉ አዲስ አበባ ዝም ብላለች። ማስተዋልና ጥበብ የሌላቸው ሁሉ ስልጣነ-መንግስቱን
ሲቀልዱበት አዲስ አበባ እንዴት እንዳስቻላት አላውቅም። ሌላም ጉድ አለ። የእግዚአብሄር ሰዎች የነበሩት ፓትርያርኮቹ
አቡነ ቴዎፍሎስ፣ አቡነ ተክለሃይማኖትና አቡነ መርቆርዮስ በታጋዩ አባ ጳውሎስ ሲተኩ ሕዝበ ክርስትያኑ በፍርሃት ተውጦ
ስልጣነ-ክህነቱንና ቅዱስ ሲኖዶሱን አስደፍሯል።
አዲስ አበባ ከየአራቱ ማዕዘናት የተሰባሰቡት የእትዮጵያ ሕዝቦች ባንድነት የሚኖሩባት ማዕከል በመሆንዋ የሀገሪቱን
ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንም ለመንግስት የምታቀርበውም እሱዋው ነች። ቀደም ሲል በመላ ሃገሪቱ የሚገኙት ተማሪዎች
የንጉሱን አስተዳደር በመቃወም እጅግ እልህ የተሞላበት ትግልን ማድረጋቸው ሲታወስ፣ ለመንግስቱ ቅርበት ያላቸው
የአዲስ አበባው ተማሪዎችም ደግሞ ስርዓቱ ማስተዳደር እስቂያቅተው ድረስ ተናንቀውታል። በወሬ የምሰማው ''መሬት
ላራሹና" - "ሕዝባዊ መንግስት" ይመስረት መፈክሮች - መፈክሮች ብቻ ሳይሆኑ የታጋዩ ልበ ሙሉነትንን ማንጸባረቅያ
የሕዝቦች ሙሉ መብት እንደነበሩ ነው። ታጋዩ በየተራ ሲሞት ጥያቄዎቹ ግን እስካሁን መልስ አላገኙም። ያለፈው ወጣት
መሬት ላራሹ በማለቱ በንጉሱ ወታደሮች ተደብድቧል ተብሏል። ቀጥሎም ሕዝባዊ መንግስት በማለቱ በደርግ ቀይ ሽብር
ተገድሏል አሉ። የዘንድሮው በኔ ዘመን የተከሰተው ለየት ያለ ነው። ወጣቱ "ስብዓዊ መብት ይከበር" - "ሕዝባዊ
መንግስትም" እንዳይል ታፍኖ ስለ ስደት ብቻ እንዲያውጠነጥን ተደርጓል። እነአንዷለም፣ እስክንድርና ርዕዮት የመሳሰሉት
ብቸኛ ቆራጦች የቀድሞውን ወጣት ታሪካዊ አደራ ተሸክመው ሕዝባዊ መንግስት በማለታቸው ቃሊቲ ተወርውረዋል።
ከላይ በጽሁፌ ላይ እንደጀመርኩት አዲስ አበባ ዛሬ የተጨናነቀችው በተፈናቃዮችና በወሮበሎች ብዛት እንጂ የልማቱ
እንቅሳቃሴ በወለዳቸው ሠራተኞች አይደለም። አዲስ አበባን ጨምሮ ሌሎች ከተሞች ሳይቀሩ በጎዳና ተዳዳሪዎች፣ በሴተኛ
አዳሪዎች፣ በልመናና በሸክም በሚተዳደሩ፣ ጥቃቅን ሥራዎችን በሚፈልጉ ችግረኞች፣ ትምህርታቸውን በጨረሱ ሥራ
አጦች፣ በቀማኞችና ማጅራት መችዎች፣ በወያኔው ደህንነቶችና ፖሊሶች፣ ከተለያዩ ሀገሮች በመጡ ሴት አሳዳጆች፣ ጎጂ
ዕጾችንና ጫትን በሽያጭ በሚያስፋፉ ወሮበሎች፣ የሀገሪቱን ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ከሀገር በሚያስወጡ ዘራፊዎች፣
ሴት እህቶቻችንን ለአረቡ ሀገራት በሚያከፋፍሉ ደላሎች፣ በኮንትሮባንድ ሥራ በተሰማሩ አታላዮች፣ ወጣቱን ለስደት
በሚያሰማሩ አስኮብላዮች፣ ወዘተ ተሞልተዋል። በንጉሱ ዘመንም ሆነ በደርግ ዘመን ሕዝቡም እንዳቅሙ በልቶ ያድር ነበር
ይባላል። ዛሬ ግን ተጠቃሚዎቹ የሀገሪቱን ኃብትና ቅርስ መዝባሪዎቹ፣ ሙስናውን ከመጠን በላይ ያደለቡት ባለስልጣኖቹና
እነሱን ተገን ያደረጉት ወገነተኛ ነጋዴዎችና ዘራፊዎች ሲሆኑ ሕዝቡ ግን በረሃብ እየተቀጣ የብቀላ ርምጃ እየተወሰደበት
ነው።
ወያኔ ብዙዎችን ከቀያቸው ወይም ከሰፈራ ጣብያቸው እያፈናቀለ በየከተሞች እንዲሰበሰቡ ያደርጋል። የጋምቤላ ሕዝብ
መሬት ለሕንዶቹ ተሰጥቷል። የኦሞ ሸለቆው ድንቅ ሕዝብ መሬት እየተቀማ ለባዕዳኑ ሊሰጥ ነው። የአፋሮቹም መሬት
በሸንኮራ እርሻ ሳብያ እየተቀማ ነው። ወያኔ ዋልድባ የመሳሰሉትን ገዳማትን በማፍረስ ክርስትያኑን ሳይቀር በማፈናቀል ላይ
ይገኛል። በበደኖና በአርባጉጉ እንዳላስጨፈጨፉት ሁሉ ከደቡብ ኢትዮጵያ ቤንች ማጂ ዞን ጉራ ፋርዳ ወረዳ ለቀህ ውጣ
በማለት ይህንኑ መከረኛ አማራ እፈናቀሉት። ይህ ሁሉ ችግረኛ ሕዝብ ከተሞችን እንዲያጨናንቅ ሆን ተብሎ የሚሰራ ራሱን
የቻለ የወያኔው ሕዝብን የማፈናቀል ሥራ ከግፍ አገዛዙ መርሃ ግብር አንዱ ነው። ዓላማው ሕዝቡ በመንግስቱ ላይ
ከመነሳቱ በፊት በወሮበሎቹና ዘራፊዎቹ እርስ በእርሱ እንዲጨራረስ የተወጠነ ሰይጣናዊ ተልዕኮ ነው። ወያኔ በቅንጅቱ
ከተሸነፈ በኋላ ውስጥ ውስጡን ሲሰራው የነበረው ይህ ሕዝቡን የማፈናቀሉ ሥራ ድህነትን በየገጠሩ ማስፋፋትና ማህበራዊ
ቅራኔዎችን በከተሞች በማባባስ የአገዛዝ ዘመኑን ማስረዘም ነው። ባጠቃላይም ወያኔ ከተሞችን እንደ ኮንሴንትሬሽን ካምፕ
በመጠቀም ገጠሪቱን ኢትዮጵያ ላባዕዳኑ ኃይል በመሸጥ ላይ ነው።
አቶ መለስ የሀገሪቱን ችገር እኮ አስቀድመው ራሳቸው ነግረውን ነበር። "እድላችን ሆኖ ጠንካራ ተቃዋሚ አላገኘንም" -
ነበር ያሉት። አባባላቸውን ጠልቆ ሲረዱት እርሳቸው ወንበሩን በመቆናጠጣቸው ተቃዎሚዎችን ማንም እንደማይረዳ
የሚጠቁም ነበር። ቀጥለውም " አዲስ አበባ ፎቅ በፎቅ ሆናለች እየተባል ከዳር ዳር ይወራል - በእርግጥ ማንም ከደረጃ
በታች የሆነ ፎቅ በዘመናዊ ፎቅ ሲተካ የማይወድ የለም - ነገር ግን ከዚህ ሁሉ ፎቅ ማህል አንድ ሶስተናው እንዱስትሪ
ቢሆን ኖሮ በልማቱ ላይ ከፍተና እድገት ያሳይ ነበር" - ብለዋል። ንግግራቸው ሕዝቡ ላይ ለማሾፍ ብቻም አይደለም። ፎቁ
በሙስና ሲገነባ ዝም ብለው ችግሩ ሲባባስ ማማሃኛ ፈለጉ። ችግሩን ወያኔ ሆን ብሎ የፈጠረው እንዳይመስል የማደናገርያ
የፖለቲካ ስልት ተጠቀሙ። ከምርጥ ንግግሮቻቸው ማህል ግን ይህን አባባላቸው ሁላችንንም የሚያነቃ መሆን ይገባዋል።
"መሬቱን ሊያለማ የሚመጣው አረቡ፣ ቱርኩና ሕንዱ ነው። ወደድንም ጠላንም ነገ ሀገር የሌለን ባይተዋር ነው
የምንሆነው" – ብለዋል። ወያኔዎቹ አስተዳደሩ ሲያቅታቸው ሀገሪቱን ለባዕድ ሸጠው ወይንም ኢትዮጵያን ለማፍረስ
ላደፈጡ ጠላቶችዋ አሳልፈው ሰጥተው ሕዝቡን ለመከራ አጋልጠው እነሱም ዶግ አመድ ሆነው እንደሚቀሩ አቶ መለስ
ተንብየው እስከወድያኛው አሸለቡ።
እድላችን እንዳይሰምር ሆኖ የሕዝባዊ መንግስት ጥያቄአችን እስካሁን መልስ ሳያገኝ ወደ ሕዝባዊ መፈናቅሉ አሸጋግሮናል።
ሕዝባዊ መፈናቅሉ ወደ ሕዝባዊ መፍረስ ሊያሸጋግረን ጥቂት ይቀራል። የዘመናቱ ባሕላዊው የዘውድ ሥርወ መንግስትና
የሀገር ሠራዊት ተንዷል፣ የሀገር ጥቅምና ሕልውና አስከባሪዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን በኢአማኞችና
ዓለማዊ ሴረኞች ተመዝብራለች። በደሙና በስጋው ዋጅቶ የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ያስጠበቀው
ኢትዮጵያዊውን ልጅና የልጅ ልጆች ማፈናቀሉና ማሰደዱ ሀገሪቱን የማፍረሱ ቀጣይ ምዕራፍ ሆኗል። ዛሬ ከመንግስት
ሥልጣን ጠያቂነት ወደ ታች ወርደን ሀገርን ወደ ማዳን ደረጃ ተሸጋግረናል። ኢትዮጵያ ስትዳከም ፈንጠዝያው
የምዕራብያኖቹ ወዲህም የአረቦቹ ነው። ወያኔ የምዕራቦቹና አረቦቹ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ እንጂ እንደ ኢትዮጵያ
ሕዝብ ተወካይ ሲሰራ አልቻለም።
ከዚህ በኋላ ምን አይነት የትግል ስልት መከተል እንደሚኖርብን ግራ ተጋብተናል። የሃገሪቱ መፍረስ ግን የደቡቡን ሕዝብ፣
ኦሮሞውን፣ ትግሬውን፣ አማራውን፣ ጋምቤላውን፣ አፋሩን፣ ኦጋዴኑን፣ ባጠቃላይም መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመለከት
ትልቅ አደጋ እንደሆን ልንረዳው ይገባናል። ጥያቄአችን የዲሞክራሲና የሕዝባዊ መንግስት መሆኖ ቀርቶ ሀገር የማዳኑ
ሆኗል።
እነዚህኑ መከራዎችና ግፎችን አስመልክቶ ብዙ ተጽፏል። ብዙ ውይይቶች ተደርገውበታል። በሀገር ቤት በሚኖሩም ሆነ
በውጭው በሚኖሩ ምሁራንም ብዙ ትችቶችና የተቃውሞ ጽሁፎች ቀርበዋል። ይህ ሁሉ የሰላም ትግል ወያኔ ሥርዓቱን
እንዲያሻሽል ወይም ሕዝብ በመረጠው መንግስት እንዲተካ ነበር። ግን ፈቀቅ ያለ ነገር የለም። የዋጋው ግሽበትና የድህነቱ
መስፋፋት ሕዝቡን አዳሽቆታል። ሕዝባችን ተሰዶ ሊያልቅ ነው።
ኢትዮጵያውያን ሁላችን ሃገር ከመፍረሷ በፊት አንድ ሃሳብ አንድ ልብ ሆነን አገርን ለማዳን በቆራጥነት እንዳይነሳ
ያላስቻለልን መንፈሳዊ ብክለት በቅጡ ልንመረምር ይገባል።
ሕዝባዊ መንግስት ስንል ስንጮህ የነበርን እንደዋዛ ሕዝብ የማፈናቀሉን የጉራፈርዳንና የቤንሻንጉሉ ፖለቲካን በአይናችን
ተመለከትን። ነገን ብንጠብቅ የባሰ ነው። ዛሬውኑ በአንድነት ተነስተን ሕዝባዊ መፍረሱን መታደግ አለብን።
በቸር እንሰንብት
ሚክያስ ሙሉጌታን በዚህ አድራሻ ማግኘት ይቻላል michyas.ethio@yahoo.com
ሚክያስ ሙሉጌታ ከ ኖርዌ
ድሮ ከዘውዱ መገርሰስ በፊት አዲስ አበባ እንደህ እንዳሁኑ ጭንቅንቅ ያላለች ለመሆኗ ትላልቆች ሲናገሩ እሰማለሁኝ። ብዙ
ሰዎች እርስ በእርሳችን እንተዋወቅ ነበር፣ ያለው ለሌለው ያዝናል፣ አውደ አመቱን በጋራ እናከብራለን ይላሉ። ቤት ገብቶ
የሚዘርፍ ሌባ ቀርቶ የተሰጣን ልብስ እንኳን ከውጭ አንስቶ የሚሰወር ወስላታ እምብዛም አይታይም ይላሉ። ሁሉም
በአቅሙ ሰርቶ ስለሚኖር የሰው እጅን መመልከት ነውር እንደነበርም ያወሳሉ። ሕዝቡ እግዚአብሄርን በጽኑ ያመልካል፣
በኢትዮጵያዊነቱ ይመካል፣ ባንዲራውን ይወዳል፣ ንጉሱንም ያከብራል፣ እያሉ ትላልቆቹ ዘወትር ሲያወሩ በጽሞና
አዳምጣለሁኝ።
እኔ የማውቃት አዲስ አበባ ግን ታላላቆቼ እንደሚያወሩላት አይደለችም። ምንድነው ምክንያቱ አልኳቸው? "ቀድሞ
ክርስትያኑና እስላሙ ተፋቅሮ የሚኖርባት፣ ባህልና ወጉ የሚናፍቁባት፣ ግብረገብነቱና ጨዋነቱ ጥልቅ የነበሩባት፣ የምሁሩ
እውቀትና የሕዝቡ ማስተውል እንደ እንቁ የሚብለጨለጩባት፣ ኪነቱ፣ ቴያትሩና ስነ ጥበቡ እውነትንና እምነትን
ሲያንጸባርቁባት የነበረችው አዲስ አበባ ዛሬ በክፋት ሠራዊትና በሙስና ባለሃብቶች በመወረሯ ነዋ" አሉኝ። በእርግጥ እኔም
እንደታዘብኩት የአዲስ አበባ መሬት ካቅሟ በላይ በስርቆት በተገነቡ ሕንፃዎች፣ በዳንኪራ ቤቶች፣ መሸታ ቤቶች፣ ቅባት
ቤቶች፣ የውበት ሳሎኖች፣ ላውንደሪዎች፣ መኪና አከራዮች፣ ወዘተ ተጨናንቃለች።
የኢጣልያ የቅኝ ገዢነት ሕልም ለማብከን መኳንንቱ የመከሩበት የእምዬ ሚኒልክና የነብር አራስዎ እቴጌ ጣይቱ መናኸርያ
ያ ታላቁ ቤተ መንግስት ኢትዮጵያን በማይወዱት ሰዎች ተይዟል። የንጉሠ ነገስቱ ኃይለሥላሴ ማደርያ ኢዮቤልዩ ቤተ
መንግስትም ተደፍሯል። ደርግ ታላላቆቹ የሀገር ኃብት የነበሩትን ወደር የለሽ ምርጥ ምሁራን ቢገድልም አብዛኛዎቹን ንጉሱ
ያስተማሯቸውን ብቁ ምሁራን ተጠቅሞባቸው ነበር። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ብቃቱ ፈጽሞ የሌላቸው የወያኔ የጫካ ሽፍቶች
የመንግስት መዋቅሩን ሲያዛንፉ አዲስ አበባ ዝም ብላለች። ማስተዋልና ጥበብ የሌላቸው ሁሉ ስልጣነ-መንግስቱን
ሲቀልዱበት አዲስ አበባ እንዴት እንዳስቻላት አላውቅም። ሌላም ጉድ አለ። የእግዚአብሄር ሰዎች የነበሩት ፓትርያርኮቹ
አቡነ ቴዎፍሎስ፣ አቡነ ተክለሃይማኖትና አቡነ መርቆርዮስ በታጋዩ አባ ጳውሎስ ሲተኩ ሕዝበ ክርስትያኑ በፍርሃት ተውጦ
ስልጣነ-ክህነቱንና ቅዱስ ሲኖዶሱን አስደፍሯል።
አዲስ አበባ ከየአራቱ ማዕዘናት የተሰባሰቡት የእትዮጵያ ሕዝቦች ባንድነት የሚኖሩባት ማዕከል በመሆንዋ የሀገሪቱን
ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንም ለመንግስት የምታቀርበውም እሱዋው ነች። ቀደም ሲል በመላ ሃገሪቱ የሚገኙት ተማሪዎች
የንጉሱን አስተዳደር በመቃወም እጅግ እልህ የተሞላበት ትግልን ማድረጋቸው ሲታወስ፣ ለመንግስቱ ቅርበት ያላቸው
የአዲስ አበባው ተማሪዎችም ደግሞ ስርዓቱ ማስተዳደር እስቂያቅተው ድረስ ተናንቀውታል። በወሬ የምሰማው ''መሬት
ላራሹና" - "ሕዝባዊ መንግስት" ይመስረት መፈክሮች - መፈክሮች ብቻ ሳይሆኑ የታጋዩ ልበ ሙሉነትንን ማንጸባረቅያ
የሕዝቦች ሙሉ መብት እንደነበሩ ነው። ታጋዩ በየተራ ሲሞት ጥያቄዎቹ ግን እስካሁን መልስ አላገኙም። ያለፈው ወጣት
መሬት ላራሹ በማለቱ በንጉሱ ወታደሮች ተደብድቧል ተብሏል። ቀጥሎም ሕዝባዊ መንግስት በማለቱ በደርግ ቀይ ሽብር
ተገድሏል አሉ። የዘንድሮው በኔ ዘመን የተከሰተው ለየት ያለ ነው። ወጣቱ "ስብዓዊ መብት ይከበር" - "ሕዝባዊ
መንግስትም" እንዳይል ታፍኖ ስለ ስደት ብቻ እንዲያውጠነጥን ተደርጓል። እነአንዷለም፣ እስክንድርና ርዕዮት የመሳሰሉት
ብቸኛ ቆራጦች የቀድሞውን ወጣት ታሪካዊ አደራ ተሸክመው ሕዝባዊ መንግስት በማለታቸው ቃሊቲ ተወርውረዋል።
ከላይ በጽሁፌ ላይ እንደጀመርኩት አዲስ አበባ ዛሬ የተጨናነቀችው በተፈናቃዮችና በወሮበሎች ብዛት እንጂ የልማቱ
እንቅሳቃሴ በወለዳቸው ሠራተኞች አይደለም። አዲስ አበባን ጨምሮ ሌሎች ከተሞች ሳይቀሩ በጎዳና ተዳዳሪዎች፣ በሴተኛ
አዳሪዎች፣ በልመናና በሸክም በሚተዳደሩ፣ ጥቃቅን ሥራዎችን በሚፈልጉ ችግረኞች፣ ትምህርታቸውን በጨረሱ ሥራ
አጦች፣ በቀማኞችና ማጅራት መችዎች፣ በወያኔው ደህንነቶችና ፖሊሶች፣ ከተለያዩ ሀገሮች በመጡ ሴት አሳዳጆች፣ ጎጂ
ዕጾችንና ጫትን በሽያጭ በሚያስፋፉ ወሮበሎች፣ የሀገሪቱን ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ከሀገር በሚያስወጡ ዘራፊዎች፣
ሴት እህቶቻችንን ለአረቡ ሀገራት በሚያከፋፍሉ ደላሎች፣ በኮንትሮባንድ ሥራ በተሰማሩ አታላዮች፣ ወጣቱን ለስደት
በሚያሰማሩ አስኮብላዮች፣ ወዘተ ተሞልተዋል። በንጉሱ ዘመንም ሆነ በደርግ ዘመን ሕዝቡም እንዳቅሙ በልቶ ያድር ነበር
ይባላል። ዛሬ ግን ተጠቃሚዎቹ የሀገሪቱን ኃብትና ቅርስ መዝባሪዎቹ፣ ሙስናውን ከመጠን በላይ ያደለቡት ባለስልጣኖቹና
እነሱን ተገን ያደረጉት ወገነተኛ ነጋዴዎችና ዘራፊዎች ሲሆኑ ሕዝቡ ግን በረሃብ እየተቀጣ የብቀላ ርምጃ እየተወሰደበት
ነው።
ወያኔ ብዙዎችን ከቀያቸው ወይም ከሰፈራ ጣብያቸው እያፈናቀለ በየከተሞች እንዲሰበሰቡ ያደርጋል። የጋምቤላ ሕዝብ
መሬት ለሕንዶቹ ተሰጥቷል። የኦሞ ሸለቆው ድንቅ ሕዝብ መሬት እየተቀማ ለባዕዳኑ ሊሰጥ ነው። የአፋሮቹም መሬት
በሸንኮራ እርሻ ሳብያ እየተቀማ ነው። ወያኔ ዋልድባ የመሳሰሉትን ገዳማትን በማፍረስ ክርስትያኑን ሳይቀር በማፈናቀል ላይ
ይገኛል። በበደኖና በአርባጉጉ እንዳላስጨፈጨፉት ሁሉ ከደቡብ ኢትዮጵያ ቤንች ማጂ ዞን ጉራ ፋርዳ ወረዳ ለቀህ ውጣ
በማለት ይህንኑ መከረኛ አማራ እፈናቀሉት። ይህ ሁሉ ችግረኛ ሕዝብ ከተሞችን እንዲያጨናንቅ ሆን ተብሎ የሚሰራ ራሱን
የቻለ የወያኔው ሕዝብን የማፈናቀል ሥራ ከግፍ አገዛዙ መርሃ ግብር አንዱ ነው። ዓላማው ሕዝቡ በመንግስቱ ላይ
ከመነሳቱ በፊት በወሮበሎቹና ዘራፊዎቹ እርስ በእርሱ እንዲጨራረስ የተወጠነ ሰይጣናዊ ተልዕኮ ነው። ወያኔ በቅንጅቱ
ከተሸነፈ በኋላ ውስጥ ውስጡን ሲሰራው የነበረው ይህ ሕዝቡን የማፈናቀሉ ሥራ ድህነትን በየገጠሩ ማስፋፋትና ማህበራዊ
ቅራኔዎችን በከተሞች በማባባስ የአገዛዝ ዘመኑን ማስረዘም ነው። ባጠቃላይም ወያኔ ከተሞችን እንደ ኮንሴንትሬሽን ካምፕ
በመጠቀም ገጠሪቱን ኢትዮጵያ ላባዕዳኑ ኃይል በመሸጥ ላይ ነው።
አቶ መለስ የሀገሪቱን ችገር እኮ አስቀድመው ራሳቸው ነግረውን ነበር። "እድላችን ሆኖ ጠንካራ ተቃዋሚ አላገኘንም" -
ነበር ያሉት። አባባላቸውን ጠልቆ ሲረዱት እርሳቸው ወንበሩን በመቆናጠጣቸው ተቃዎሚዎችን ማንም እንደማይረዳ
የሚጠቁም ነበር። ቀጥለውም " አዲስ አበባ ፎቅ በፎቅ ሆናለች እየተባል ከዳር ዳር ይወራል - በእርግጥ ማንም ከደረጃ
በታች የሆነ ፎቅ በዘመናዊ ፎቅ ሲተካ የማይወድ የለም - ነገር ግን ከዚህ ሁሉ ፎቅ ማህል አንድ ሶስተናው እንዱስትሪ
ቢሆን ኖሮ በልማቱ ላይ ከፍተና እድገት ያሳይ ነበር" - ብለዋል። ንግግራቸው ሕዝቡ ላይ ለማሾፍ ብቻም አይደለም። ፎቁ
በሙስና ሲገነባ ዝም ብለው ችግሩ ሲባባስ ማማሃኛ ፈለጉ። ችግሩን ወያኔ ሆን ብሎ የፈጠረው እንዳይመስል የማደናገርያ
የፖለቲካ ስልት ተጠቀሙ። ከምርጥ ንግግሮቻቸው ማህል ግን ይህን አባባላቸው ሁላችንንም የሚያነቃ መሆን ይገባዋል።
"መሬቱን ሊያለማ የሚመጣው አረቡ፣ ቱርኩና ሕንዱ ነው። ወደድንም ጠላንም ነገ ሀገር የሌለን ባይተዋር ነው
የምንሆነው" – ብለዋል። ወያኔዎቹ አስተዳደሩ ሲያቅታቸው ሀገሪቱን ለባዕድ ሸጠው ወይንም ኢትዮጵያን ለማፍረስ
ላደፈጡ ጠላቶችዋ አሳልፈው ሰጥተው ሕዝቡን ለመከራ አጋልጠው እነሱም ዶግ አመድ ሆነው እንደሚቀሩ አቶ መለስ
ተንብየው እስከወድያኛው አሸለቡ።
እድላችን እንዳይሰምር ሆኖ የሕዝባዊ መንግስት ጥያቄአችን እስካሁን መልስ ሳያገኝ ወደ ሕዝባዊ መፈናቅሉ አሸጋግሮናል።
ሕዝባዊ መፈናቅሉ ወደ ሕዝባዊ መፍረስ ሊያሸጋግረን ጥቂት ይቀራል። የዘመናቱ ባሕላዊው የዘውድ ሥርወ መንግስትና
የሀገር ሠራዊት ተንዷል፣ የሀገር ጥቅምና ሕልውና አስከባሪዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን በኢአማኞችና
ዓለማዊ ሴረኞች ተመዝብራለች። በደሙና በስጋው ዋጅቶ የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ያስጠበቀው
ኢትዮጵያዊውን ልጅና የልጅ ልጆች ማፈናቀሉና ማሰደዱ ሀገሪቱን የማፍረሱ ቀጣይ ምዕራፍ ሆኗል። ዛሬ ከመንግስት
ሥልጣን ጠያቂነት ወደ ታች ወርደን ሀገርን ወደ ማዳን ደረጃ ተሸጋግረናል። ኢትዮጵያ ስትዳከም ፈንጠዝያው
የምዕራብያኖቹ ወዲህም የአረቦቹ ነው። ወያኔ የምዕራቦቹና አረቦቹ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ እንጂ እንደ ኢትዮጵያ
ሕዝብ ተወካይ ሲሰራ አልቻለም።
ከዚህ በኋላ ምን አይነት የትግል ስልት መከተል እንደሚኖርብን ግራ ተጋብተናል። የሃገሪቱ መፍረስ ግን የደቡቡን ሕዝብ፣
ኦሮሞውን፣ ትግሬውን፣ አማራውን፣ ጋምቤላውን፣ አፋሩን፣ ኦጋዴኑን፣ ባጠቃላይም መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመለከት
ትልቅ አደጋ እንደሆን ልንረዳው ይገባናል። ጥያቄአችን የዲሞክራሲና የሕዝባዊ መንግስት መሆኖ ቀርቶ ሀገር የማዳኑ
ሆኗል።
እነዚህኑ መከራዎችና ግፎችን አስመልክቶ ብዙ ተጽፏል። ብዙ ውይይቶች ተደርገውበታል። በሀገር ቤት በሚኖሩም ሆነ
በውጭው በሚኖሩ ምሁራንም ብዙ ትችቶችና የተቃውሞ ጽሁፎች ቀርበዋል። ይህ ሁሉ የሰላም ትግል ወያኔ ሥርዓቱን
እንዲያሻሽል ወይም ሕዝብ በመረጠው መንግስት እንዲተካ ነበር። ግን ፈቀቅ ያለ ነገር የለም። የዋጋው ግሽበትና የድህነቱ
መስፋፋት ሕዝቡን አዳሽቆታል። ሕዝባችን ተሰዶ ሊያልቅ ነው።
ኢትዮጵያውያን ሁላችን ሃገር ከመፍረሷ በፊት አንድ ሃሳብ አንድ ልብ ሆነን አገርን ለማዳን በቆራጥነት እንዳይነሳ
ያላስቻለልን መንፈሳዊ ብክለት በቅጡ ልንመረምር ይገባል።
ሕዝባዊ መንግስት ስንል ስንጮህ የነበርን እንደዋዛ ሕዝብ የማፈናቀሉን የጉራፈርዳንና የቤንሻንጉሉ ፖለቲካን በአይናችን
ተመለከትን። ነገን ብንጠብቅ የባሰ ነው። ዛሬውኑ በአንድነት ተነስተን ሕዝባዊ መፍረሱን መታደግ አለብን።
በቸር እንሰንብት
ሚክያስ ሙሉጌታን በዚህ አድራሻ ማግኘት ይቻላል michyas.ethio@yahoo.com