Wednesday, December 16, 2015

ልብ በሉ፦

ልብ በሉ፦ ወያኔን ማስወገድ ያለብን የቅኝ ገዢዎች ተባባሪዎች፣ ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት፣ ክብርና ታሪክ
ፈጽሞ የማይጨነቁ፣ ሃገሪቱን ወደብ አልባ ያደረጉ፣ ኃይማኖትን የበከሉ፣ ሕዝቡን ለስደት ሞትዕና ለዳግም
ክፉ ቀን የዳረጉ ሰው መሰል ጨካኝ አራዊቶች ስለሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በኢንተርኔት፣ ፓልቶክ፣ ሬድዮና
ቴሌቪዥን በሚተላለፍ ትግልዕ ብቻ አይሞከርም። ዛሬ በአቶ መለስ የሙት መንፈስ ምስል እየተመራ
በመበታተኑ ጣዕረ ሞት የሚያቃስተውን ወያኔን ገፍትረን መጣል ካልቻልን ነገ አገግሞ ለሌላ መቅሰፍት
ይዳርገናል።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

Sunday, December 6, 2015

የአቶ መለስ ራዕይ 2

የአቶ መለስ ራዕይ 2
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

Thursday, December 3, 2015

የአቶ መለስ ራዕይ


የአቶ መለስ ራዕይ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስደፈረ፣ ኅልውናዋን የተፈታተነ፣ ታሪኳን ያንቋሸሸ ደረቅ ራዕይዕ ነዉ።
ራዕዩ የሕንድና የአረብ ከበርቴዎችን ያስፈነጠዘ፣ ሼሁንና ሎሌዎቹን ያወፈረ፣ የቅኝ ገዢዎችን ምኞት ያሳካ፣ በርካታ ቀን የሰጣቸውን
ባለስልጣናትና ዘመዶቻቸውን ያባለገ ራዕይ ነበር። በአለም ባንክ ርዳታ የተነጠፈው ጎዳና ረጅም - ግን ደረቅ
የሙስናውንና የኤፈርቱን የዘረፋ ሸቀጥ በተሸከሙ ከባድ መኪኖች የተጨናነቀ ጎዳና ነው። በየመስኩ
የተንጣለሉት ሌብነትና ጉቦ ወለድ ፋብሪካዎቹ የሕዝቡን ኑሮ አላሽቀውታል። ራዕዩ ሃይማኖትን ሳይቀር
የተፈታተነ ሕዝብን ያጠወለገ የክፋት ምንጭ ነበር። ዛሬ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ቀድሞ ተንሰራፍቶ የነበረው
ሙስና ገሃድ ወጥቶ ሙስናውያኑን እያባረረ ነው። በቅርቡ በኦሮምያና ትግራይ ክልሎች ባሉ ትልቁ የሙስና
ዋሻ የመሸጉ ሁሉ ሙቅ ውሃ እንደተደፋባቸው አይጦች ይራወጣሉ። የስባዓዊ መብት ጥሰቱ ይቁም (Stop
human rights violation)፣ አምባገነንነት ይውደም (Down with Dictatorship)፣ ሙስናው ያብቃ (Stop
Corruption)፣ የሚሉ ሰላማዊ መፈክሮች ይዘን ስለወጣን ለስደት የዳረጉን ከቀበሌ እስከ መንግስት አመራር
ያሉ ሁሉ ነገ ተጠያቂዎች ናቸው።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

Monday, November 30, 2015

ሠማይ ጠቅስ ሕንፃዎች ተደርድረዋል ይባላል። ሠፊው ጎዳና የሠማዩን አድማስ አቋርጧል ይባላል። ወንዙ
ተገድቦ ውሃው ተንጣሎ ተኝቷል ይባላል። ማዶ ከተራራው ሥር ዘመናዊ የእርሻ ልማት ይታያል ይባላል።
የእድገቱ አሃዝ ጨምሮ የሕዝቡ ኑሮ መሻሻሉን የሚዘግብ ዶኩሜንተሪ ፊልም በቴሌቪዥን ይታያል። የአቶ
መለስ ራዕይ ሠምሯል ማለት ይሆን? - ግናስ ሀገሬ ኢትዮጵያ ምን ነካት? – ምነው ኩርምት አለች? – ምነው
ገጿ ደበዘዘ?