Thursday, December 24, 2015

የመስመር ልዩነት የሌላቸው ፖለቲካ ፓርቲዎች በቶሎ ወደ አንድነቱ
መምጣት አለባቸው። ለሃገሪቱ ርጥብ ራዕይ ያላቸው ድርጅቶች ሁሉ መቀራረብ አለባቸው። ኢትዮጵያ
የምታገግመው ከትግሉ ሜዳ በተለያዩ ምክንያት የራቁትን ጀግኖቿን በፍቅር ተማጽኖ ትግሉን እንደገና
እንዲቀላቀሉ ሲደረግ ነው። ማዕከላችን ኢትዮጵያ ነች። ሁላችንም ለኢትዮጵያ እናስባለን። ልዩነታችን
ውበታችን ነው። አንድነታችን አምባገነንነትን ያንበረክካል። ሙስናን ያጠፋል። ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መብት
የማይረገጥባት ሀገር ትሆናለች።

አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።




Friday, December 18, 2015

How Corrupt Is Ethiopia?

ትግላችንን ተጠናክሮ በአንድነት ይቀጥል!

December 17, 2015
def-thumbየኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ በያቅጣጫው መነሳቱ የሚያኮራ ነው። ባለፉት 3 ዓመታት ብቻ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ያደረጉትን የመብት ትግል ጨምሮ በደቡብ፣ አማራ፣ አፋር፣ ጋምቤላና በሌሎችም አካባቢዎች በርካታ የነጻነት ትግሎች ተካሂደዋል። አሁን በኦሮምያ እና በአማራ በተለይም በሰሜን ጎንደር አካባቢዎች እየተካሄዱ ያሉት የነጻነት ትግሎች የአጠቃላዩ የነጻነት ትግል አካሎች ናቸው። በእነዚህ የነጻነት ትግሎች ገዢው ፓርቲ ከህዝብ ጋር ለምንጊዜውም መለያየቱን ለማየት ችለናል። ስልጣኑን ለማስጠበቅ ሲልም፣ አቅሙ ቢፈቅድለትና ማግኘት ቢችል በምድር ላይ ያሉትን ጅምላ ጨራሽ መሳሪያዎችን ሁሉ በገዛ ህዝቡ ላይ ለመጠቀም ወደ ሁዋላ የማይል የአረመኔዎች ስብስብ መሆኑን አረጋግጠናል። በጭካኔውና በፍርሃቱ ብዛት የተነሳ በርካታ ሙስሊሞች፣ ክርስቲያኖች፣ መብታቸውን በሰላም ለመጠየቅ ወደ አደባባይ የወጡ ወጣቶች ተገድለዋል፤ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ጋዜጠኞች በእስር ተንገላተዋል፤ በእስር ቤትም ማንነታቸውን ከማዋረድ ጀምሮ የተለያዩ አካላዊ ጥቃቶች ተፈጽሞባቸዋል።
የኦሮሞ ህዝብ መብቴ ይከበርልኝ ብሎ መነሳቱን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ከያቅጣጫው ድጋፋቸውን እየገለጹ ነው። ይህ ለነጻነት ሃይሎች ብስራት ሲሆን ዘርን ከዘር በማጋጨት የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ለሚፈልገው የሽፍታ አገዛዝ ደግሞ ትልቅ መርዶ ነው። ባለፉት 25 ዓመታት ወያኔ አንዱን ዘር ከሌላው ዘር እያጋጨ፣ በወንድማማቾችና እህትማማቾች መካከል መተማመን እንዳይፈጥር መርዙን ሲረጭ ቆይቷል፤ ያሰበው አልሰምርለት ሲል ደግሞ በአገሪቱ አንጡራ ሃብት በሸመተው ጠመንጃ ለመብቱ የተነሳውን ህዝብ ደረት ደረቱን እየመታ ፈጅቶታል። በተለይም የአማራው ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር በአንድነት ተሰልፎ በህወሃት አገዛዝ ላይ የነጻነት ክንዱን ለማሳረፍ እንዳይችል ሌት ተቀን የጥላቻ መርዙን በመርጨት ከሌላው ህዝብ ጋር እንዲጋጭ ለማድረግ በእጅጉ ደክሟል። ወያኔ የረጨውን የጥላቻ መርዝ የኦሮሞ እና የአማራ ልጆች በጋራ እያረከሱት መገኘታቸው፣ የሌሎች ብሄሮችና ብሄረሰቦች ህዝቦችም እንዲሁ ” አንለያይም” በማለት በጋራ ለመሰለፍና ትግሉን ለማቀጣጠል ዝግጁነታቸውን መግለጻቸውና በተግባር እያሳዩ መምጣታቸው የ25 አመታት የወያኔ የአፈናና የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ እያከተመ መምጣቱን የሚያመላክት ነው። ወያኔ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲው በመላው ኢትዮጵያውያን ትብብር እንደረከሰበት ሲያውቅ ደግሞ የግድያ አዋጅ አውጥቶ በ-ኢትዮጵያውያኑ ላይ ጥይት አርከፍክፎ ጸጥ ሊያሰኛው መዘጋጀቱን በአዋጅ አስነግሯል። ከታሪክ መማር የማይችለው ጠባቡ ወያኔ፣ ህዝባቸውን አዋጅ አስነግረው የገደሉ ጨቋኝ መንግስታት መጨረሻቸው ምን እንደነበረ እንኳን ቆም ብሎ ማሰብ አልቻለም። ዛሬ የእሳት ላንቃ በሚተፋ ጠመንጃቸው ሊጨፈልቀው የሚያስበው ህዝብ ነገ መልሶ ራሱን እንደሚጨፈልቀው ለአፍታም ቢሆን ለማሰላሰል አልቻለም። የዘረፈው ሃብትና የታጠቀው መሳሪያ አእምሮውን ደፍኖት፣ እየመጣ ያለውን ህዝባዊ ሱናሚ ለማየት ተስኖታል። በጦር መሳሪያ ጋጋታና ድንፋታ ቢሆን ኖሮ ወራሪዋ ጣሊያን እስከዛሬ ድረስ ከአገራችን ለቃ ባልወጣች ነበር፣ በጦር መሳሪያ ጋጋታ ቢሆን ኖሮ እነ ጋዳፊን ዛሬ ቤተመንግስት እንጅ መቃብር ውስጥ አናገኛቸውም ነበር።
የአገራችን ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለነጻነቱ የሚያደርገውን ትግል በጥንቃቄ የሚመራበት ጊዜ ላይ ነን ። የገጠመን ጠላት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ፣ የገዛ ህዝቡን በጠላትነት ፈርጆ ሊያጠፋው የተነሳ በመሆኑ፣ አገዛዙ እስከዛሬ ካደረሰው ጥፋት ሌላ ተጨማሪ ጥፋት ሳያጠፋ፣ ከአገራችን መሬት ለመንቀል እንድንችል እርምጃችን ሁሉ ጥንቃቄ የተሞላበት ሊሆን ይገባል። ጠላታችን ህዝብን ከህዝብ ለማፋጀት ያለ የሌለ ሃይሉን የሚጠቀም መሆኑ ብቻ ሳይሆን፣ አቅሙ በፈቀደለት መጠን ሁሉ ህዝቡን በጅምላ ለመፍጀት ወደ ሁዋላ የማይል ነው። ህዝቡ የጠላቱን አውሬነት ተገንዝቦ እሱ በሚከፍተው ቀዳዳ ዘው ብሎ ላለመግባት መጠንቀቅ አለበት። ሊገድሉን ሲመጡ ዘወር ብሎ በማሳለፍ፣ እንደገና ደግሞ ወደ አደባባይ በመውጣት፣ እንዲሁም የተቃውሞውን አድማስ በማስፋትና የሃይል መከፋፈል እንዲፈጠር በማድረግ ወያኔን አዳክሞና ተስፋ አስቆርጦ ካለሙት ግብ መድረስ ይቻላል። አሁን እየታየ ያለው አንድነት ይበልጥ እየተጠናከረ፣ ከኦሮሞው ጎን አማራው፣ ከአማራው ጎን ጉራጌው፣ ከጉራጌው ጎን ትግሬው፣ ከትግሬው ጎን አፋሩ፣ ከአፋሩ ጎን ጋምቤላው፣ ከጋምቤላው ጎን ሀረሪው፣ ከሃረሪው ጎን ጉሙዙ፣ ከጉሙዙ ጎን አዲስ አበቤው፣ ከአዲስ አበቤው ጎን ጋሞው በአጠቃላይ መላው ህዝብ እጅ ለእጅ እየተያያዘ የነጻነት ባበሩ ወደፊት እንዲሮጥ ማድረግ አለበት። ወጣቱ ራሱን ባለበት ቦታ እያደራጀና አመራር እየሰጠ በያቅጣጫው የጀመረውን የነጻነት ትግል አጠናክሮ ይቀጥል።
አርበኞች ግንቦት7 ትግሉን በተለያዩ አቅጣጫዎች አጠናክሮ ቀጥሎአል፤ የአርበኛው ሰራዊት የወያኔን ጀሌዎች በቀኝና በግራ መውጫና መግቢያ እያሳጣቸው ነው። የንቅናቄው አባላት በዳር አገር በአፈሙዝ፣ በመሃል አገር ደግሞ ወጣቱን እያደራጁ ለትግል እንዲሰልፍ እያደረጉት ነው። የንቅናቄያችን መሪ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ፣ “ከነጻነት ትግሎች ጎን አለን” እንዳሉት የአርበኛው ልጆች ፊት ለፊት ተሰልፈው አመራር በመስጠት የነጻነት ትግሉን ለማቀጣጠል እና መከፈል ያለበትን የህይወት መስዋትነት ለመክፈል ተዘጋጅተው በያቅጣጫው እየተንቀሳቀሱ ነው።
ተደጋግሞ እንደተነገረው የአርበኞች ግንቦት7 አላማ በአገራችን የዲሞክራሲያዊ የሽግግር ስርዓት ማስጀመር ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በዚህ አላማ ዙሪያ ተሰልፎ ትግሉን ይቀጥል። ይህን አላማ የሚደግፉ የፖለቲካ ድርጅቶችም ዛሬውኑ ከጎናችን ተሰልፈው ወያኔን ለማስወገድ በሚደረገው የሞት ሽረት ትግል ይሰለፉ!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!
አገራችን በልጆቿ ነጻ ትወጣለች!
አርበኞች ግንቦት7

ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍበ ኖርዌ ኦስሎ ከተማ ተደረገ

በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን የወያኔ መንግስት በኦሮሞ ተማሪዎች ላይ ያደረሰውን ኢሰብአዊ ግድያ እና በምዕራብ ኢትዮጵይ በጎንደር ክልል ለሱዳን ተላልፎ የሚሠጠውን መሬት ምክንያት በመቃወም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍበ ኖርዌ ኦስሎ ከተማ ተደረገ።

Wednesday, December 16, 2015

ልብ በሉ፦

ልብ በሉ፦ ወያኔን ማስወገድ ያለብን የቅኝ ገዢዎች ተባባሪዎች፣ ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት፣ ክብርና ታሪክ
ፈጽሞ የማይጨነቁ፣ ሃገሪቱን ወደብ አልባ ያደረጉ፣ ኃይማኖትን የበከሉ፣ ሕዝቡን ለስደት ሞትዕና ለዳግም
ክፉ ቀን የዳረጉ ሰው መሰል ጨካኝ አራዊቶች ስለሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በኢንተርኔት፣ ፓልቶክ፣ ሬድዮና
ቴሌቪዥን በሚተላለፍ ትግልዕ ብቻ አይሞከርም። ዛሬ በአቶ መለስ የሙት መንፈስ ምስል እየተመራ
በመበታተኑ ጣዕረ ሞት የሚያቃስተውን ወያኔን ገፍትረን መጣል ካልቻልን ነገ አገግሞ ለሌላ መቅሰፍት
ይዳርገናል።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

Sunday, December 6, 2015

የአቶ መለስ ራዕይ 2

የአቶ መለስ ራዕይ 2
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

Thursday, December 3, 2015

የአቶ መለስ ራዕይ


የአቶ መለስ ራዕይ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ያስደፈረ፣ ኅልውናዋን የተፈታተነ፣ ታሪኳን ያንቋሸሸ ደረቅ ራዕይዕ ነዉ።
ራዕዩ የሕንድና የአረብ ከበርቴዎችን ያስፈነጠዘ፣ ሼሁንና ሎሌዎቹን ያወፈረ፣ የቅኝ ገዢዎችን ምኞት ያሳካ፣ በርካታ ቀን የሰጣቸውን
ባለስልጣናትና ዘመዶቻቸውን ያባለገ ራዕይ ነበር። በአለም ባንክ ርዳታ የተነጠፈው ጎዳና ረጅም - ግን ደረቅ
የሙስናውንና የኤፈርቱን የዘረፋ ሸቀጥ በተሸከሙ ከባድ መኪኖች የተጨናነቀ ጎዳና ነው። በየመስኩ
የተንጣለሉት ሌብነትና ጉቦ ወለድ ፋብሪካዎቹ የሕዝቡን ኑሮ አላሽቀውታል። ራዕዩ ሃይማኖትን ሳይቀር
የተፈታተነ ሕዝብን ያጠወለገ የክፋት ምንጭ ነበር። ዛሬ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ቀድሞ ተንሰራፍቶ የነበረው
ሙስና ገሃድ ወጥቶ ሙስናውያኑን እያባረረ ነው። በቅርቡ በኦሮምያና ትግራይ ክልሎች ባሉ ትልቁ የሙስና
ዋሻ የመሸጉ ሁሉ ሙቅ ውሃ እንደተደፋባቸው አይጦች ይራወጣሉ። የስባዓዊ መብት ጥሰቱ ይቁም (Stop
human rights violation)፣ አምባገነንነት ይውደም (Down with Dictatorship)፣ ሙስናው ያብቃ (Stop
Corruption)፣ የሚሉ ሰላማዊ መፈክሮች ይዘን ስለወጣን ለስደት የዳረጉን ከቀበሌ እስከ መንግስት አመራር
ያሉ ሁሉ ነገ ተጠያቂዎች ናቸው።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።

Monday, November 30, 2015

ሠማይ ጠቅስ ሕንፃዎች ተደርድረዋል ይባላል። ሠፊው ጎዳና የሠማዩን አድማስ አቋርጧል ይባላል። ወንዙ
ተገድቦ ውሃው ተንጣሎ ተኝቷል ይባላል። ማዶ ከተራራው ሥር ዘመናዊ የእርሻ ልማት ይታያል ይባላል።
የእድገቱ አሃዝ ጨምሮ የሕዝቡ ኑሮ መሻሻሉን የሚዘግብ ዶኩሜንተሪ ፊልም በቴሌቪዥን ይታያል። የአቶ
መለስ ራዕይ ሠምሯል ማለት ይሆን? - ግናስ ሀገሬ ኢትዮጵያ ምን ነካት? – ምነው ኩርምት አለች? – ምነው
ገጿ ደበዘዘ?

Sunday, November 29, 2015

ወያኔ ሰራሽ የርስበርስ ግጭት ድግሶችን እናምክን

ወያኔ ሰራሽ የርስበርስ ግጭት ድግሶችን እናምክን

November 28, 2015
def-thumbየወያኔ ስርዓት የኢትዮጵያን አስተዳደር ሲያዋቅር በህዝብ ታሪካዊ አብሮነትና ተዛምዶ ላይ ተመስርቶ ሳይሆን የብሔር ብሔረሰብ ልዩነቶችን በማጉላትና ልዩነቱም የርስበርስ ጥርጣሬና ግጭት ምንጭ እንዲሆን በማድረግ ነው። ልዩነቱ የእርስ በርስ ግጭትና የረጅም ጊዜ ቁርሾ እንዲፈጥር ተደርጎ ከመዋቀሩ በተጨማሪ፣ ግጭቱ በማንኛውም ጊዜ እንዲነሳ ፖለቲካዊ ግፊት ይደረግበታል ። አንዱ ብሔረሰብ በሌላው ብሔረሰብ ክልል ውስጥ ሲሆን ባዕድነት እንዲሰማውና እንዲሰጋ፣ አንዱ ሌላውን በጥርጣሬ እንዲመለከተው ለማድረግ ላለፉት 24 አመታት ሲገፋ ቆይቷል፤ እየተገፋም ነው። በዘመነ ወያኔ በየቦታው በብሔር ወይም ብሔርሰብ ስም የተነሱ ግጭቶች በሙሉ የተቀሰቀሱት በራሱ በአገዛዙ ባለስልጣኖች እንጂ በህዝቡ አይደለም፤ ሆኖም አያውቅም። በተለያዩ የደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች የአማራ ተወላጆችን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ለማባረር የተወሰዱት እርምጃዎች በሙሉ ባለስልጣኖቹ ከፊትና ከጀርባ ሆነው የቀሰቀሱዋቸው ፣ ያቀነባበሩዋቸውና የመሩዋቸው ለመሆናቸው ተጎጂዎች በግልጽ ሲናገሩ ሰምተናል።
በቅርቡ በቤኒሻጉል ጉሙዝ ክልል ውስጥ በአስቃቂ ሁኔታ ተገድለውና ተጥለው የተገኙት የአማራ ተወላጆች የሥርዓቱን ባህሪይ ከሚያሳዩ መግለጫዎች አንዱ ነው ። እንዲህ አይነቱ አሰቃቂ ድርጊት ወያኔ ባስለጠናቸውና ባዘዛቸው ካድሬዎችና ባለስልጣኖች የተፈጸመ እንጂ በሕዝብ ተነሳሽነት የተፈጸመ አለመሆኑ ግልጽ ነው። በቅርብ የተፈጸመው ድርጊት ቀደም ሲል በመንግስት ደረጃ የተቀነባበረው አማሮችን የማፈናቀል ዘመቻ ተከታይ ስራ ነው። በወገኖቻችን ላይ በሚዘገንን መንገድ የተፈጸመው ይህ አሰቃቂ ግፍ ዘልቆ ይሰማናል። ቁጭታችንና ሀዘናችን ግን ወያኔ ወደሚፈልገው የሕዝብ ለሕዝብ ግጭት መንስኤ እንዳይሆን ከፍተኛ ትዕግስትና ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል።
ሰሞኑን እንደገና በታሪክ ሊዘገብ ከሚችል ልዩነት ውጭ ባኗኗር፣ በባህልና ቋንቋ የማይለያዩትን የሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች ቅማንትና አማራ በሚል ለማጋጨት ጥረት በማደረግ ላይ ይገኛል። ይህ ሰይጣናዊ አካሔድ በወያኔ የፖለቲካ ተንኮል እየተመራ እንዳለ የሚያሳዩ ብዙ መረጃዎች አሉ። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ካላንዳች መድሎና ልዩነት ሀገሪቱ ላይ መብታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ሁሉም በየበኩላቸው የሚያደርጉትን ጥረትና ትግል ይደግፋል። በህዝባችን መካከል ያሉት ግንኙነቶች አንዱ አንዱን የሚያግዝና የሚደግፍ እንዲሆን እንጂ የእርስ በርስ የመጋጨትም ሆነ የመናቆር ምክንያት እንዳይሆን ተግቶ ይሠራል ።
ኢትዮጵያውያን ብሄርና ዘር ሳንለያይ ይህንን የወያኔ ተንኮል ችግሩ ወደባሰ ደረጃ ሳይሄድ መቋቋምና ማክሸፍ እንደሚኖርብን አርበኞች ግንቦት 7 ያሳስባል። ይህ ታሪክዊ መተሳሰራችንንና ታላቅ ሕዝብነታችንን የማይመጥን አሳፋሪ የወያኔ ፖለቲካ እንደሀገር እንዳያጠፋን ሁላችንም በንቃትና በቁርጠኝነት መቋቋም ይኖርብናል::
አርበኞች ግንቦት ፯ ልዩነት ጌጥ እንጂ የጠብና የግጭት ምክንያት የማይሆንባት ሀገር ፥ የየብሔረሰቡ መብት ሁሉ የይስሙላ ሳይሆን በተግባር የተረጋገጠባት ሀገር ፥ ከነልዩነታችን በጋራ ራዕይ የምንተሳሰርባትና የምንገነባት ሀገር እንድትኖረን የሚያደርገውን ትግል ይቀጥላል። የቻልክ በአካል ተቀላቀለን። ያልቻልክ በያለህበት የወያኔ ዘራፊዎች ያሰቡትን የተንኮል ጉንጉን በመበጣጠስ ተሳተፍ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !

"ደረቅ ራዕይ" - "ደረቅ ትግል" - Zehabesha Amharic

"ደረቅ ራዕይ" - "ደረቅ ትግል" - Zehabesha Amharic
ላለፉት 24 አመታት በየቦታው ለተነሱት የ ጎሣ ግጭቶች መንስኤው እራሱ ወያኔ እንጂ ህዝቡ አይደለም።
ሰሞኑንም ወያኔ የ ሰሜን ኢትዮጽያ ህዝቦችን ቅማንት ና አማራ በሚል ለማጋጨ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል
ስለሆነም ሁሉም ኢትዮጵያዊ በአንድነት የወያኔን ተንኮል ከወዲሁ ማክሸፍ አለብን።

Wednesday, October 7, 2015

"ሕዝባዊ መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቀልወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ»
ሚክያስ ሙሉጌታ ግዛው ከኖርዌ
«People's government, People's Displacenet” or People's Disfranchisement
by M.M.G
Translated from Amharic
I heard from elders that Addis Ababa (AA) was not crowded as it is today. Many people knew each other. Many people look after one another. And many people used to celebrate festivals together. There were no thieves entering houses or even clothes were not disappeared from dryer outside. All adults have a work to earn a living depending of their profession. No one depend on the hand of the other. All believes in God and were proud of Ethiopia. All loves the flag, gave respect to the King. This was what I heard from the elders.
AA which I know today is not the same as AA which I heard from my elders. What is the reason? I asked. In the past Moslems and Christians lived in harmony. In the past traditions and customs went alongside in harmony. Moral and manners were deep whereas knowledge of intellectuals was shining like jewels. During the past, drama and arts reflected truths and beliefs. AA today is besieged by traitors and corrupted businessmen. Of-course AA is full of corruption buildings, night clubs, bars, cosmetics, beauty salons, laundries, car renters and so on.
The palace which was once stood as counseling house of the patriots, where King Menelik and Taitu discussed how to conquer colonialism, is taken by banditries which do not care for Ethiopia. The jubilee palace of King Hailesselassie is also occupied. The military rule (DERG) killed intellectuals but meanwhile used the knowledge of intellects that had the chance to get best education during the kingdom of Haile Selassie. Today, it is different. Illiterates, who do hate Ethiopia, are dancing in the great palaces, AA remain silent. Today while those gangsters’ without knowledge and wisdom are playing with the power of the people, AA still sited silence. I do not know why? There is also another amazing factor. When the Abunas (His Holiness – Patriarchs or Spiritual Heads of the Ethiopian Orthodox Church) Theophilos and Tekle Haymanot are replaced by the revolutionary priest Aba Paulos, AA remains passive because of fear. Tragically when the power of the spiritual fathers and the legal Synods is misused, AA remains silent. It is really a shame.
AA is the capital city where people from around the country are coming to live together. AA is the capital city engaged in bringing political demands to the state. During the monarchy, students in AA opposed the rule of the king. It was AA which trembles the throne of the king. There after the king was not capable of administering the country. The slogans «LAND TO THE TILLER» and «PEOPLE'S GOVERNMENT NOW» were not only slogans. They were directives and symbol of the revolutionary students. They were indeed peoples rights. Revolutionaries deceased but the slogans are still alive. Astonishingly, we still have no answer for these revolutionary demands. During previous times, the youth was beaten by sticks for raising these demands. Then students were murdered by red terror squads of the military regime for repeating these questions. Today the phenomena in my age are different. We, the youth cannot raise these demands. We are pushed by the government to flee instead of saying «RESPECT HUMAN RIGHTS» or «PEOPLES GOVERNMENT». Courageous Ethiopians such as Andualem Arage, Esikindre and Riot are thrown into prison only for echoing the past demands of the people.
AA, as I have mentioned it above, is currently crowded by either displaced persons (from native places) or looters. They are not workers to get hired in the industries, to earn for a living. AA including other cities in Ethiopia are full of street children, prostitutes, thieves and looters, graduated unemployed and depressed youths, state security agents, polices, sex hunters, narcotic sellers, illegal vendors of ancient antiques, dealers to send girls to Arab countries, contrabandists and smugglers. During the times of the past regimes people were eating at least 3 times. Today those who are eating are only the looters, corrupting officials and their friends. The people are starving. This is revenge politics of the TPLF.
Old demand such as «PEOPLE'S GOVERNMENT» which is not still answered turned to be «PEOPLE'S DISPLACEMENT». I am afraid that «PEOPLE'S DISPLACEMENT» will turn to «PEOPLE'S DISFRANCHISEMENT». The traditional log age rule of dynasties and its modern army destroyed. The patriotic Ethiopian Orthodox Church has been ruined (taken by atheists). The next stage remained is to lose Ethiopia and migrate. The old demands such as «people's government» are no more political demands. We are not able to fight for it right now. We should give priority to defend the sovereignty of the country instead. When we are weak Westerners or Arabs might be happy. TPLF, which is favored by westerners, is in power.
It is becoming vague to us whether what kind or struggle we should follow. But one thing we realized is that the destruction of Ethiopia will be a big shame to the Oromos, Tigres, Amharas, Gambellas, Afars, Ogadens and all the rest of Ethiopians. Tragically we remain to defend the unity of Ethiopia rather than demanding democracy or people's government.
Many words are already written about what I try to explain here. Many discussions have been performed. All these attempts were in order that TPLF will improve its bad rule or replace TPLF with people's representatives. But nothing has changed. High food prices (inflation) and poverty weaken the people's hope. All are migrating.
We Ethiopians should discuss about the reason why we could not stand together as one people.
We, Ethiopians, were shouting for «PEOPLES GOVERNMENT». But on the contrary we saw with our own eyes that indigenous people are displaced from native lands, such as Guraferda and Benshangul. What is remaining? We should get up and stand up as one, before we, the people, are shattered into pieces.
Let us remain healthy.
MMG

Monday, September 28, 2015

“ደረቅ ራዕይ” – “ደረቅ ትግል” | Zehabesha Amharic

“ደረቅ ራዕይ” – “ደረቅ ትግል” | Zehabesha Amharic

"ደረቅ ራዕይ" - "ደረቅ ትግል"
ሚኪያስ ሙሉጌታ ግዛው ከኖርዌ
ሠማይ ጠቅስ ሕንፃዎች ተደርድረዋል ይባላል። ሠፊው ጎዳና የሠማዩን አድማስ አቋርጧል ይባላል። ወንዙ
ተገድቦ ውሃው ተንጣሎ ተኝቷል ይባላል። ማዶ ከተራራው ሥር ዘመናዊ የእርሻ ልማት ይታያል ይባላል።
የእድገቱ አሃዝ ጨምሮ የሕዝቡ ኑሮ መሻሻሉን የሚዘግብ ዶኩሜንተሪ ፊልም በቴሌቪዥን ይታያል። የአቶ
መለስ ራዕይ ሠምሯል ማለት ይሆን? - ግናስ ሀገሬ ኢትዮጵያ ምን ነካት? – ምነው ኩርምት አለች? – ምነው
ገጿ ደበዘዘ?
የአቶ መለስ ራዕይ ሉዓላዊነቷን ያስደፈረ፣ ኅልውናዋን የተፈታተነ፣ ታሪኳን ያንቋሸሸ "ደረቅ ራዕይ" ስለነበር
ነዋ። እምዪ ኢትዮጵያ ምነው ታድያ ኩርምት አትል? ምነው ገጿ አይደበዝዝ`? ራዕዩ የሕንድና የአረብ
ከበርቴዎችን ያስፈነጠዘ፣ ሼሁንና ሎሌዎቹን ያወፈረ፣ የቅኝ ገዢዎችን ምኞት ያሳካ፣ በርካታ ቀን የሰጣቸውን
ባለስልጣናትና ዘመዶቻቸውን ያባለገ ራዕይ ነበር። በአለም ባንክ ርዳታ የተነጠፈው ጎዳና ረጅም - ግን ደረቅ
የሙስናውንና የኤፈርቱን የዘረፋ ሸቀጥ በተሸከሙ ከባድ መኪኖች የተጨናነቀ ጎዳና ነው። በየመስኩ
የተንጣለሉት ሌብነትና ጉቦ ወለድ ፋብሪካዎቹ የሕዝቡን ኑሮ አላሽቀውታል። ራዕዩ ሃይማኖትን ሳይቀር
የተፈታተነ ሕዝብን ያጠወለገ የክፋት ምንጭ ነበር። ዛሬ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ቀድሞ ተንሰራፍቶ የነበረው
ሙስና ገሃድ ወጥቶ ሙስናውያኑን እያባረረ ነው። በቅርቡ በኦሮምያና ትግራይ ክልሎች ባሉ ትልቁ የሙስና
ዋሻ የመሸጉ ሁሉ ሙቅ ውሃ እንደተደፋባቸው አይጦች ይራወጣሉ። የስባዓዊ መብት ጥሰቱ ይቁም (Stop
human rights violation)፣ አምባገነንነት ይውደም (Down with Dictatorship)፣ ሙስናው ያብቃ (Stop
Corruption)፣ የሚሉ ሰላማዊ መፈክሮች ይዘን ስለወጣን ለስደት የዳረጉን ከቀበሌ እስከ መንግስት አመራር
ያሉ ሁሉ ነገ ተጠያቂዎች ናቸው።
በእርግጥ ሙስናው ያደለባቸው አምባገነኖች ደረቅ ተቃውሞን አይፈሩም። ደረቅ ከደረቅ ቢጋጭ ለውጥ
እንደማይመጣ ተንኮሉን ጫካ እያሉ አውጠንጥነውታል። አምባገነኖቹ ደረቅ ወሬን፣ ደረቅ ጽሁፍን፣ ደረቅ
ጩኸትን፣ ደረቅ አመጽን አይፈሩም። ደረቅና ውሸት ጋጋታዎች የእድሜአቸው ማራዘምያ ኪኒኖች ናቸው።
ወያኔነዎቹ በበርሃ ላይ ድንገት ፍልቅ እንደምትለው ምንጭ ርጥብ ነገርን ከተመለከቱ ነው ክው የሚሉት።
ታድያ መልሰው እስኪያደርቋት ድረስ እንቅልፍ አይወስዳቸውም። ዓይነተኛ ባህርያቸው ይህ ነው። ወያኔዎች
እስክንድር ነጋንና አንዷለምን እንደ ጦር ይፈራሉ። ወደፊት ሌላ እስክንድርና አንዷለም ዓይነቶች
እንዳያብቡም ነው ዛሬ በሰማያዊ፣ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ የሚያደርጉት። አቶ
መለስን ትንሿ የእስክንድር የብዕር ጠብታ ለፍርሀቱ ስትዳርጋቸው - የአበበ ገላው ድምጽ ደግሞ ኃይል
አግኝቶ አንገታቸውን አስደፍቷቸው ነበር።
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ። ብቻ ፍርዱን ለእግዚአብሔር
እንተወው።
የሚያሳዝነው ታድያ እስካሁን ድረስ በአቶ መለስ መተት ለተቀሰፈው የውስጡም የውጭውም ደረቅ ትግል
ማርጠብያ መድሃኒት አለመገኘቱ ነው። መፈክሮቻችን፣ ሰልፎቻችን፣ ስብሰባዎቻችን፣ ጽሑፎቻችን የታንክ
ጥይት ቢሆኑ ኖሮ የሕወሀት ዘመን አጭር በሆነ ነበር። እንደተዋጊ ጄቶች የፈጠኑት ድኅረ ገጾች፣ ጋዜጦችና
መጽሄቶች ቦንብ ተሸካሚዎች ቢሆኑ ኖሮ ሕወሀትና ሻዕቢያ መቀመቅ ወርደው ሕዝቦች ነጻ በወጡ ነበር።
በገቡ በጥቂት ቀናት መወገድ ስለነበረባቸው ኢሕአዲጋውያን በማውሳት ሕዝቡ - "ሳንፈልጋቸው ሀያ
ሞላቸው" – በማለት ብሶቱን አች አምና በታላቁ ሩጫ ወቅት አሰምቷል። ትግሉ እጅግ ለመዘግየቱ ከዚህ ሌላ
ምን ማስረጃ አለ?
የአቶ መለስ መንፈስ በተቃዋሚው ጎራ ሳይቀር ሰርጎ ገብቶ ተግባር በሌለው ምላሳቸው ሰብዓዊ መብት
ተገፈፈ፣ ምርጫው ተዛባ፣ ሙስና ተስፋፋ፣ ዲሞክራሲ የለም - እያሉ የሚያስተጋቡ ልሳናቸው የኢትዮጵያን
ክብር የማያውጅ ደረቅ አስመሳይ ተባባሪዎችን ሳይቀር አፋፍቷል። ባጠቃላይ "ደረቅ ትግሉ" የኢትዮጵያ
የቀድሞ ክብሯና ገናናነትዋ ዳግም እንዳይመለስ ለሚፈልጉት ምዕራብያውያን እፎይታ፣ ለኢሕአዲጎቹ እድሜ
ማራዘምያ ኪኒን፣ ለሻዕቢያ - ለኦነግና ለአልሻባብ ጊዜ መግዢያ አሞሌ ጨው እንዲሁም በዝርፊያና በወንጀል
ተጠያቂ ለሆኑት ግለሰቦች ሽፋን ሠጪ ተኩስ ከመሆን በቀር ለኢትዮጵያና ለሕዝቦቿ አፋጣኝ መድህን መሆን
አልቻለም፣።
ልብ በሉ! ኢሕአዲጎቹን ማስወገድ ያለብን የቅኝ ገዢዎች ተባባሪዎች፣ ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት፣ ክብርና ታሪክ
ፈጽሞ የማይጨነቁ፣ ሃገሪቱን ወደብ አልባ ያደረጉ፣ ኃይማኖትን የበከሉ፣ ሕዝቡን ለ"ስደት ሞት"ና ለ"ዳግም
ክፉ" ቀን የዳረጉ ሰው መሰል ጨካኝ አራዊቶች ስለሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በኢንተርኔት፣ ፓልቶክ፣ ሬድዮና
ቴሌቪዥን በሚተላለፍ "ደረቅ ትግል" ብቻ አይሞከርም። ዛሬ በአቶ መለስ የሙት መንፈስ ምስል እየተመራ
በመበታተኑ ጣዕረ ሞት የሚያቃስተውን ኢሕአዲግ ገፍትረን መጣል ካልቻልን ነገ አገግሞ ለሌላ መቅሰፍት
ይዳርገናል። እንዲህ ተበታትነን፣ መስዋዕትነት የከፈሉትን ጀግኖች ገለል እያደረግን፣ ለወንጀለኞችና ለበታኞች
ፍሪዳ እያረድን፣ የጓደኝነቱን፣ የአበልጅነቱን፣ የሚዜነቱን "ስውር አብዮት" በየመሸታው እያጠናከርን - በደረቅ
ትግሉ ብቻ ተቃውሞን ከቀጠልን የሀገሪቱ መጪ እድል መገነጣጠል፣ መፈረካከስ - የሕዝቡ ዕጣ ደግሞ
መራብ መታረዝ ብሎም - የ"ስደትን ሞት" - እንደ ብቸኛ አማራጭ አድርጎ መቀበል ብቻ ነው።
ወያኔን ለማስወገድ መፍትሄው አንድ ብቻ ነው። መፍትሄው የመንፈስ ፅናት ነው። እንደ አለፈው ትውልድ
የጠላት ፈረስና ሰረገላ ማኅተማቸውን ሳያላላ፣ በእግዚአብሄር ኃይል ራሳቸውን አበርትተው፣ በባህሩ በደረቅ
መሬት፣ በሸለቆና በተራራው ተሰማርተው የሃገሬን ቁስለቷን እንደ ሻሩላት ጀግኖች ምሳሌ ለመሆን አስቀድሞ
የፅናቱ ቅባ ቅዱስ እንዲነካን በይቅር ባይነትና ፍቅር ዳግም መደራጀት ይኖርብናል። ፅናት አቋምን
ትወልዳለች። ውጤት የምናመጣው የሕዝብ ወገን የሆንን ሁሉ በሕብረት ተደራጅተን እንደ አንድ ሰው ሆነን
ስንታገል ብቻ ነው።
አለበለዝያማ ጽናትን የሚያጎለብተውን፣ የጀግኖቹን ፈለግ መከተሉን ትተን፣ ጋጋታና አጀብ ስናበጃጅ ዘመኑ
በከንቱ እንዳያልፍ እንጠንቀቅ። የመስመር ልዩነት የሌላቸው ፖለቲካ ፓርቲዎች በቶሎ ወደ አንድነቱ
መምጣት አለባቸው። ለሃገሪቱ ርጥብ ራዕይ ያላቸው ድርጅቶች ሁሉ መቀራረብ አለባቸው። ኢትዮጵያ
የምታገግመው ከትግሉ ሜዳ በተለያዩ ምክንያት የራቁትን ጀግኖቿን በፍቅር ተማጽኖ ትግሉን እንደገና
እንዲቀላቀሉ ሲደረግ ነው። ማዕከላችን ኢትዮጵያ ነች። ሁላችንም ለኢትዮጵያ እናስባለን። ልዩነታችን
ውበታችን ነው። አንድነታችን አምባገነንነትን ያንበረክካል። ሙስናን ያጠፋል። ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መብት
የማይረገጥባት ሀገር ትሆናለች።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።
አድራሻዬ michyas.ethio@yahoo.com ነው።

Ethio peace and politics : "ሕዝባው መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቅል" ወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ"ሚክያስ ሙ...

Ethio peace and politics : "ሕዝባው መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቅል" ወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ" ሚክያስ ሙ...: "ሕዝባው መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቅል" ወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ" ሚክያስ ሙሉጌታ ከ ኖርዌ ድሮ ከዘውዱ መገርሰስ በፊት አዲስ አበባ እንደህ እንዳሁኑ ጭንቅንቅ ያላለች...
አርበኞች ግንቦት ሰባትና ሊቀመንበሩ ዶክተር ብርሃኑ ነጋከሚክያስ ሙሉጌታ ግዛው
ዶክተር ብርሃኑ ነጋ በወጣትነታቸው ዘመን እንደማንኛውም ወጣት በተማሪው ንቅናቄ የተሰለፉ፣ የኢሕአፓ የወጣቱ ክንፍ አባል በመሆንም ደርግን የታገሉ ኋላም ወደ ሱዳንና አሜሪካ የተሰደዱ የነጻነት ትግሉ አባወራ ናቸው። ዶክተር ብርሃኑ ደርግ ወድቆ ወያኔ ስልጣኑን ሲይዝ ሕዝቡን እውጭ ባካበቱት ልምድ ለማገልገል ፈቅደው ወደ ሃገራቸው ተመልሰው በዩኒቨርሲቲ ከማስተማር ጀምሮ በቅንጅት ፓርቲ ውስት በአመራሩ ውስጥ ጉልህ ተዋናይ እስከመሆን ድረስ አገልግለዋል። ቅንጅት አምባገነኑን ሥርዓት በሠላማዊ መንገድ በመታገል በአፍሪካ ምድር ለመጀመርያ ጊዜ ሕዝባዊ ምርጫ አሸናፊነቱን እንዲጎናጸፍ የበኩላቸውን አስተዋጾ አድርገው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ እንዲሆኑ የተመረጡት ዶክተር ብርሃኑ ሥልጣኑን በሰላም ለማስረከብ ፍቃደኛ ባልሆነው ወያኔ ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር በእስር ቤት ተወርውረዋል። ከወራት እስር በኋላ የተፈቱት ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ወደ አሜሪካ ተመለሱ።
ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ወያኔ ስልጣኑን በሠላማዊ መንገድ ለማስረከብ ባህርይው እንደማይፈቅድለት ከተረዱ በኋላ ግንቦት ሠባት የዲሞክራሲንና ፍትህ ንቅናቄን፣ ከሌሎች ጓዶች ጋር በመሆን መሥርተው ሲያደራጁና በፋይናንስ ሲያጠናክሩ ቆይተው በቅርቡ ከአርበኞች ግንባር ጋር የተዋሃደውን የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄን ፍልሚያ ሊመሩ ወደ ኤርትራ ምድር ተጉዘዋል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ወደ አስመራ ሲጓዙ የመን ላይ በወያኔ የተጠለፉት ሌላኛው ግንቦት ሰባትን አምጠው የወለዱ የኢትዮጵያ አንጡራ ልጅ ናቸው።
ዶክተር ብርሃኑ ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ የተለዩ አለመሆናቸውን ዘወትር ይናገራሉ። መማር ለሀገር ሕልውና ካልበጀ፣ ሕዝቡን ቀና ካላደረገ የጋን ውስጥ መብራት ሆኖ እንደሚቀር በየስብሰባው ይገልጻሉ። ዶክተር ብርሃኑን የሚያረካቸው የነጻነት ትግል እንጂ የሥልጣን መዳረሻው ወንበር ምቾት አይደለም። ይህ የዶክተር ብርሃኑ ነጋ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ብሎም ለመምራት ወደ ኤርትራ ጉዞ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሥልጣን ትግሉ ረዥም ጉዞ አንድ አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ መክፈቱ ብቻ ሳይሆን ግንቦት ሰባት ለሕዝብ የገባውን ቃል ኪዳን ተራ በተራ መተግበሩን ይመሰክራል።
ወያኔ በሠላማዊ ትግሉ ፈጽሞ ስልጣኑን ማስረከብ እንደማይችል መረጋገጡ ሕዝቡ በአንድ ልብ የትጥቅ ትግሉን እንዲደግፍ ያደርገዋል። የአርበኞች ግንቦት ሰባት የሠሞኑ ማጥቃት ከትጥቅ ትግሉ በቀር ሌላ ፖለቲካዊ አማራጭ እንደሌለ በጽኑ ስለሚያሳይ ዳር የቆሙም ሆነ ፖለቲካ በሩቁ የሚሉ ሁሉ ሃገራዊ ድርሻቸውን ለማበርከት ይነሳሳሉ። የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ሠፊ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ከስደቱ ውርደት ይልቅ የጦር ሜዳውን ጀግንነት ይመርጣሉ። ሳይወድ በግድ የወያኔውን ስልጣን አስጠባቂ የሆኑት የመከላከያ ሠራዊቱና የፖሊስ አባላት ሕዝባዊውን ትግል በፍቅር ይቀላቀላሉ። ሌላው ቀርቶ የሙስናው ጥቅም ተቋዳሾች የሆኑት ባለስልጣኖቹና ዘመዶቻቸው ሳይቀሩ ስህቶቻቸውን አርመው፣ የበደሉትን ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀው ወያኔን አንቅረው በመትፋት የዘረፉትን የሕዝብ ሃብት በውዴታ ይመልሳሉ።  
መልካም ፖለቲካ በሰዎች አመለካከት ላይ የተንሰራፉ ብዥታዎችን ታጠራለች። ፖለቲካ አይታመንም፣ አሜሪካ ተቀምጦ ትግል የለም፣ ወዘተ፣ ዓይነቶቹ ግራ አጋቢ ብዥታዎችን እያጠሩ፣ የትጥቅ ትግሉን በማደራጀት ወያኔን መሪር የሆነ ቀውስ ውስጥ የከተተው ብሎም ከሕዝብ ወገን ከተውጣጣው ጦር ጋር እንዲላተም ያደረገው እንደነ ዶክተር ብርሃኑ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌና መሠሎቻቸው ያበረከቱት ትዕግስትንና ብስለትን የተላበሰው በሳል የፖለቲካ ሂደት ነው። ፖለቲካ እጅግ ተለዋዋጭ መሆኗ ብቻ ሳይሆን አስተማሪም ነች። በአንክሮ ለተመራመራት ፖለቲካ የትላንቱን ስህተት አጉልታ እያሳየች ወደ ተሻለው አቅጣጫ የምትመራ ምስጢራው ኮምፓስ ነች። በአንክሮ ማየት የተሳነው ደግሞ ሁልጊዜ ወደ ታች፣ ወደ ቁልቁለቱ ይጓዛል። መልካም ፖለቲካ ትክክለኛውን መንገድ ስትጠቁም ሙስና ደግሞ ልቦናን ጋርዳ ወደ ገደሉ ታዳፋለች። እብሪተኛውን ወያኔ ባዶ ያስቀረው አላዋቂ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ከጀርባው ልትወርድ ያልቻለችው አታላዩዋ፣ አዘናጊዋ ሙስና ነች። ወያኔው በሙስና የገነባውን ሕንጻ አንጋጦ ሲያይ ወይም ምቾቱ በተደላደለው እጅግ ውድ ዘመናዊ አውቶሞቢሉ ሲንሸራሸር አልያም ከፍ ዝቅ በሚለው አረግራጊው በኤሌክትሪክ ኃይል በሚሞቀውና በሚቀዘቅዘው ፍራሽ ላይ እንደተኛ ሕዝባዊው ሱናሜ ከተፍ ይልበታል።
የሁለት አስር ዓመቶቹ መልካምና ሠላማዊ የፖለቲካ ክንውኖች እንዲሁም ከታሪክ ሂደት መማር ያልቻለው "የመቶ ፐርሰንቱአሸናፊው ወያኔው ግትር ባህርይ ይህን የትጥቅ ትግል ወልዷል። ፍልሚያው በግለሰቦች አስተሳሰብ ላይ ሠፍነው የነበሩትን አንዳንድ ጥርጣሬዎች አስወግዶ መላውን ሕዝብም ሆነ የፖለቲካ ንቅናቄዎችን እንዲሁም የትግል ግንባሮችን በቅጡ ያዋህዳል።
ሁሉም በጦርነት ተሠልፎ ተዋጊ ሊሆን አይችልም። ጀግንነት፣ ተጋድሎና መስዋዕት ለመክፈል ከፊት መቅደም ከእግዚአብሄር የሚበረከት ፀጋ ነው። ወታደርነት እልህ አስጨራሽ፣ ጀግንነት ደግሞ ከጽናት የምትመነጭ አኩሪ ተግባር ነች። ሁላችንም በዚህ አኩሪ ተግባር ውስጥ መሰለፍ ባንችልም እንኳን ደጀን መሆን አያቅተንም። መናቆርን፣ መጠላለፉን አስወግደን ሁላችንም ፊታችንን ወደ ጦሩ ግንባር በማዞር የሞራል፣ የቁሳቁስና የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅብናል። በአንድም በሌላም ከመሳተፍ ተቆጥቦ የነጻነቱን ትግል አለመቀላቀል ወይም ወስልቶ መቅረት በግለሰቡ ዓዕምሮ ላይ ህፍረት ሆና ተለጥፋ የምትቀር የታሪክ ጥላሸት ነች። ይህች በሁሉም መስክ ክብር የነበራት ውድ ኢትዮጵያችንን ያዋረደውን ወያኔን መፋለም ታላቅ ክብር ነው።
በአርበኞች ግንቦት ሠባት አባልነት ተመዝግበን ትግሉን የመቀላቀል እድል የተጎናጸፍን ሁሉ ሌሎችም የኛን አርዓያ ተከትለው ሃገራዊ ድርሻቸውን የማበርከቱ እድል እንዲገጥማቸው ልባዊ ምኞታችንን እንገልጻለን። በዚህም ይሁን በዚያኛው መሰለፍ፣ የነጻነት ትግሉን የሚያግዝ አንዲት ጠጠር መወርወር ወይም የሕዝቡን መሠረታዊ መብቶች የሚያስጠብቀውን ትግል ከመቀላቀል የበለጠ ሌላ ጣፋጭ ነገር የለም።
አርበኞች ግንቦት ሰባት ያሸንፋል፤ ሕዝብ ያሸንፋል፤ አምባገነንነት በትግል ይወገዳል

Wednesday, August 5, 2015

በዛሬው ኢሳት ሬዲዮ ስርጭት

በዛሬው ኢሳት ሬዲዮ ስርጭት
_ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ በውስጥ ሽኩቻ ተጠምዷል።የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ ኢትዮጵያን ከመጎብኘታቸው አስቀድሞ የተጀመረው የእርስ በእርስ ፍጥጫ እየከረረ መጥቷል። በአቶ መለስ የተወገዱት የቀድሞ የህወሀት አመራሮች እንዲመለሱና ህወሀትን እንዲያጠናክሩ የቀረበው ሀሳብ የፍጥጫው አንዱ ምክንያት ነው ተብሏል። 
_የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስርዓቱን እየከዱ ወጥተው በሚቀሩ ዲፕሎማቶች ምትክና በሌሎች ቦታዎች የ71 ዲፕሎማቶች ምደባ ሊያደርግ መሆኑ ተገለጸ። ትላንት ኢሳት እንደዘገበው 6 ዲፕሎማቶች ስርዓቱን ከድተዋል። ከጥቂት ወራት በፊትም ከሎሳንጀለስ ቆንስላ ጽ/ቤት ወ/ሮ የሀረር ወርቅ በቀለ የተባሉ ዲፕሎማት የስራ ጊዜያቸው ቢጠናቀቅም እዚሁ ቀርተዋል። በደቡብ ኮሪያ ሴዑል የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ዶክተር ዲባባ አብደታ ወደ አዲስ አበባ መጠራታቸውም ታውቋል። ምክንያቱ አልተገለጸም።
_ድምጻችን ይሰማ የትላንቱን የፍርድ ቤት ውሳኔ ድራማ ሲል አጣጣለው። የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ለተጠናከረ ትግል እንዲዘጋጁ ጥሪ አድርጓል። አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ የፍርድ ቤቱን ውሳኔ በተመለከተ ባወጣው መግለጪያ በደሉ የሁሉም ኢትዮጵያዊ በደል ነው ብሏል። እጅ ለእጅ ተያይዘን ህወሀትን እናስወግድም ሲል አርበኞች ግንቦት ሰባት ጥሪ አስተላልፏል።
_በሸዋና በወሎ ድርቅ ገብቷል። ዝናብ የለም። ባለስልጣናት በፓርቲ ስብሰባ ተጠምደዋል። በሰሜን ሸዋ በዋግ ህምራና በወሎ በርካታ አከባቢዎች ድርቅ ተከስቷል። በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ከዝናብ አለመከሰት ጋር ተያይዞ ተመሳሳይ አደጋ እንዳንዣበበ መረጃዎች ያመለክታሉ። በአንጻሩ የህወሀት የልማት ዲስኩር ተጠናክሮ ቀጥሏል።http://ethsat.com/?p=33903

Thursday, July 23, 2015

አርበኞች ግንቦት ሰባትና ሊቀመንበሩ ዶክተር ብርሃኑ ነጋ


አርበኞች ግንቦት ሰባትና ሊቀመንበሩ ዶክተር ብርሃኑ ነጋከሚክያስ ሙሉጌታ ግዛው
ዶክተር ብርሃኑ ነጋ በወጣትነታቸው ዘመን እንደማንኛውም ወጣት በተማሪው ንቅናቄ የተሰለፉ፣ የኢሕአፓ የወጣቱ ክንፍ አባል በመሆንም ደርግን የታገሉ ኋላም ወደ ሱዳንና አሜሪካ የተሰደዱ የነጻነት ትግሉ አባወራ ናቸው። ዶክተር ብርሃኑ ደርግ ወድቆ ወያኔ ስልጣኑን ሲይዝ ሕዝቡን እውጭ ባካበቱት ልምድ ለማገልገል ፈቅደው ወደ ሃገራቸው ተመልሰው በዩኒቨርሲቲ ከማስተማር ጀምሮ በቅንጅት ፓርቲ ውስት በአመራሩ ውስጥ ጉልህ ተዋናይ እስከመሆን ድረስ አገልግለዋል። ቅንጅት አምባገነኑን ሥርዓት በሠላማዊ መንገድ በመታገል በአፍሪካ ምድር ለመጀመርያ ጊዜ ሕዝባዊ ምርጫ አሸናፊነቱን እንዲጎናጸፍ የበኩላቸውን አስተዋጾ አድርገው የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ እንዲሆኑ የተመረጡት ዶክተር ብርሃኑ ሥልጣኑን በሰላም ለማስረከብ ፍቃደኛ ባልሆነው ወያኔ ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር በእስር ቤት ተወርውረዋል። ከወራት እስር በኋላ የተፈቱት ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ወደ አሜሪካ ተመለሱ።
ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ወያኔ ስልጣኑን በሠላማዊ መንገድ ለማስረከብ ባህርይው እንደማይፈቅድለት ከተረዱ በኋላ ግንቦት ሠባት የዲሞክራሲንና ፍትህ ንቅናቄን፣ ከሌሎች ጓዶች ጋር በመሆን መሥርተው ሲያደራጁና በፋይናንስ ሲያጠናክሩ ቆይተው በቅርቡ ከአርበኞች ግንባር ጋር የተዋሃደውን የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄን ፍልሚያ ሊመሩ ወደ ኤርትራ ምድር ተጉዘዋል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ወደ አስመራ ሲጓዙ የመን ላይ በወያኔ የተጠለፉት ሌላኛው ግንቦት ሰባትን አምጠው የወለዱ የኢትዮጵያ አንጡራ ልጅ ናቸው።
ዶክተር ብርሃኑ ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ የተለዩ አለመሆናቸውን ዘወትር ይናገራሉ። መማር ለሀገር ሕልውና ካልበጀ፣ ሕዝቡን ቀና ካላደረገ የጋን ውስጥ መብራት ሆኖ እንደሚቀር በየስብሰባው ይገልጻሉ። ዶክተር ብርሃኑን የሚያረካቸው የነጻነት ትግል እንጂ የሥልጣን መዳረሻው ወንበር ምቾት አይደለም። ይህ የዶክተር ብርሃኑ ነጋ የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ብሎም ለመምራት ወደ ኤርትራ ጉዞ በኢትዮጵያ ሕዝብ ሥልጣን ትግሉ ረዥም ጉዞ አንድ አዲስ ታሪካዊ ምዕራፍ መክፈቱ ብቻ ሳይሆን ግንቦት ሰባት ለሕዝብ የገባውን ቃል ኪዳን ተራ በተራ መተግበሩን ይመሰክራል።
ወያኔ በሠላማዊ ትግሉ ፈጽሞ ስልጣኑን ማስረከብ እንደማይችል መረጋገጡ ሕዝቡ በአንድ ልብ የትጥቅ ትግሉን እንዲደግፍ ያደርገዋል። የአርበኞች ግንቦት ሰባት የሠሞኑ ማጥቃት ከትጥቅ ትግሉ በቀር ሌላ ፖለቲካዊ አማራጭ እንደሌለ በጽኑ ስለሚያሳይ ዳር የቆሙም ሆነ ፖለቲካ በሩቁ የሚሉ ሁሉ ሃገራዊ ድርሻቸውን ለማበርከት ይነሳሳሉ። የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ሠፊ ፍላጎት ያላቸው ወጣቶች ከስደቱ ውርደት ይልቅ የጦር ሜዳውን ጀግንነት ይመርጣሉ። ሳይወድ በግድ የወያኔውን ስልጣን አስጠባቂ የሆኑት የመከላከያ ሠራዊቱና የፖሊስ አባላት ሕዝባዊውን ትግል በፍቅር ይቀላቀላሉ። ሌላው ቀርቶ የሙስናው ጥቅም ተቋዳሾች የሆኑት ባለስልጣኖቹና ዘመዶቻቸው ሳይቀሩ ስህቶቻቸውን አርመው፣ የበደሉትን ሕዝብ ይቅርታ ጠይቀው ወያኔን አንቅረው በመትፋት የዘረፉትን የሕዝብ ሃብት በውዴታ ይመልሳሉ።  
መልካም ፖለቲካ በሰዎች አመለካከት ላይ የተንሰራፉ ብዥታዎችን ታጠራለች። ፖለቲካ አይታመንም፣ አሜሪካ ተቀምጦ ትግል የለም፣ ወዘተ፣ ዓይነቶቹ ግራ አጋቢ ብዥታዎችን እያጠሩ፣ የትጥቅ ትግሉን በማደራጀት ወያኔን መሪር የሆነ ቀውስ ውስጥ የከተተው ብሎም ከሕዝብ ወገን ከተውጣጣው ጦር ጋር እንዲላተም ያደረገው እንደነ ዶክተር ብርሃኑ፣ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌና መሠሎቻቸው ያበረከቱት ትዕግስትንና ብስለትን የተላበሰው በሳል የፖለቲካ ሂደት ነው። ፖለቲካ እጅግ ተለዋዋጭ መሆኗ ብቻ ሳይሆን አስተማሪም ነች። በአንክሮ ለተመራመራት ፖለቲካ የትላንቱን ስህተት አጉልታ እያሳየች ወደ ተሻለው አቅጣጫ የምትመራ ምስጢራው ኮምፓስ ነች። በአንክሮ ማየት የተሳነው ደግሞ ሁልጊዜ ወደ ታች፣ ወደ ቁልቁለቱ ይጓዛል። መልካም ፖለቲካ ትክክለኛውን መንገድ ስትጠቁም ሙስና ደግሞ ልቦናን ጋርዳ ወደ ገደሉ ታዳፋለች። እብሪተኛውን ወያኔ ባዶ ያስቀረው አላዋቂ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ከጀርባው ልትወርድ ያልቻለችው አታላዩዋ፣ አዘናጊዋ ሙስና ነች። ወያኔው በሙስና የገነባውን ሕንጻ አንጋጦ ሲያይ ወይም ምቾቱ በተደላደለው እጅግ ውድ ዘመናዊ አውቶሞቢሉ ሲንሸራሸር አልያም ከፍ ዝቅ በሚለው አረግራጊው በኤሌክትሪክ ኃይል በሚሞቀውና በሚቀዘቅዘው ፍራሽ ላይ እንደተኛ ሕዝባዊው ሱናሜ ከተፍ ይልበታል።
የሁለት አስር ዓመቶቹ መልካምና ሠላማዊ የፖለቲካ ክንውኖች እንዲሁም ከታሪክ ሂደት መማር ያልቻለው "የመቶ ፐርሰንቱአሸናፊው ወያኔው ግትር ባህርይ ይህን የትጥቅ ትግል ወልዷል። ፍልሚያው በግለሰቦች አስተሳሰብ ላይ ሠፍነው የነበሩትን አንዳንድ ጥርጣሬዎች አስወግዶ መላውን ሕዝብም ሆነ የፖለቲካ ንቅናቄዎችን እንዲሁም የትግል ግንባሮችን በቅጡ ያዋህዳል።
ሁሉም በጦርነት ተሠልፎ ተዋጊ ሊሆን አይችልም። ጀግንነት፣ ተጋድሎና መስዋዕት ለመክፈል ከፊት መቅደም ከእግዚአብሄር የሚበረከት ፀጋ ነው። ወታደርነት እልህ አስጨራሽ፣ ጀግንነት ደግሞ ከጽናት የምትመነጭ አኩሪ ተግባር ነች። ሁላችንም በዚህ አኩሪ ተግባር ውስጥ መሰለፍ ባንችልም እንኳን ደጀን መሆን አያቅተንም። መናቆርን፣ መጠላለፉን አስወግደን ሁላችንም ፊታችንን ወደ ጦሩ ግንባር በማዞር የሞራል፣ የቁሳቁስና የፋይናንስ ድጋፍ ማድረግ ይጠበቅብናል። በአንድም በሌላም ከመሳተፍ ተቆጥቦ የነጻነቱን ትግል አለመቀላቀል ወይም ወስልቶ መቅረት በግለሰቡ ዓዕምሮ ላይ ህፍረት ሆና ተለጥፋ የምትቀር የታሪክ ጥላሸት ነች። ይህች በሁሉም መስክ ክብር የነበራት ውድ ኢትዮጵያችንን ያዋረደውን ወያኔን መፋለም ታላቅ ክብር ነው።
በአርበኞች ግንቦት ሠባት አባልነት ተመዝግበን ትግሉን የመቀላቀል እድል የተጎናጸፍን ሁሉ ሌሎችም የኛን አርዓያ ተከትለው ሃገራዊ ድርሻቸውን የማበርከቱ እድል እንዲገጥማቸው ልባዊ ምኞታችንን እንገልጻለን። በዚህም ይሁን በዚያኛው መሰለፍ፣ የነጻነት ትግሉን የሚያግዝ አንዲት ጠጠር መወርወር ወይም የሕዝቡን መሠረታዊ መብቶች የሚያስጠብቀውን ትግል ከመቀላቀል የበለጠ ሌላ ጣፋጭ ነገር የለም።
አርበኞች ግንቦት ሰባት ያሸንፋል፤ ሕዝብ ያሸንፋል፤ አምባገነንነት በትግል ይወገዳል

Sunday, July 19, 2015

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ነአምን ዘለቀ አዳዲስ ፎቶዎች ከአስመራ (ይናገራል ፎቶ)

  • 2790
     
    Share
ትናንት ዘ-ሐበሻ በሰበር ዜና ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ነአምን ዘለቀ አስመራ መግባታቸውን መዘገባችን ይታወሳል:: በዚህ መሰረት የነዚህ አመራሮች ፎቶ ግራፎች ከአስመራ ደርሰውናል::
ዶ/ር ብርሃኑ ኤርትራ በገባ በጥቂት ሰዓታት ልዩት የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ፖለቲካ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል ወደሚገኝበት ቦታ በማምራት ከህዝብ ግንኙነት ክፍሉ አርበኛ ታጋዮች ጋር ምሳ በልተዋል:: ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ለህዝብ ግንኙነት ክፍሉ አርበኛ ታጋዮች ባስተላለፉት መልዕክት
“ከሁሉም ነገር ዓላማ ያስተሳሰረው ስለሚልቅ፤ ለእኔ ለአገሩ ህይወቱን መሰዋዕት ለማድረግ ከተዘጋጀ ሰው የሚበልጥ ምንም ነገር በምድር ላይ ባለመኖሩ ወደ እናንተ መጥቻለሁ፡፡ የመጣሁትም እናንተን ለማስተማር ሳይሆን ከእናንተ ለመማር ነው… ለነፃነታችን አብረን እንሞታለን…” ብለዋል::
Birhanu Nega asmera
Birhanu nega asmera er
Birhanu nega photo
Birhanu Nega Bonger G7
G7 Birhanu nega
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/45185#sthash.kwAKZktj.dpuf

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ነአምን ዘለቀ አዳዲስ ፎቶዎች ከአስመራ (ይናገራል ፎቶ) | Zehabesha Amharic

የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና ነአምን ዘለቀ አዳዲስ ፎቶዎች ከአስመራ (ይናገራል ፎቶ) | Zehabesha Amharic

Wednesday, May 27, 2015

Patriotic Ginbot 7 (PG7) is medicament
አርበኞች ግንቦት ሰባት መድኅን ነው
by M.M. from Norway 
(Translated from Amharic)
Our country went through 50 years of torturous periods. As I understood from history, it was misery and wretchedness that brought coup attempts and political movements during the rule of the monarchy. The revolution which was erupted in the country was the outcome of all these dissatisfaction. Promising to bring a better life, the military government (DERG), who wiped out the monarchy, made the problem four times worse than the previous. As fighting between the DERG and oppositions intensified several thousands were killed and imprisoned while others were forced to migrate. In addition to the absence of democracy; the endless war, migration, and poverty, turned the land of Ethiopia into abyss. Meanwhile, the new ethnic affiliated regime (TPLF), seized power promising to end all atrocities performed by the military rule. The problem however could not be terminated. TPLF continued to carry on the same atrocities that were executed by the military rule. TPLF is in power for 24 years with a sophisticated high cruel system of oppression. This new action of oppressions that is amalgamated with racism intensified the problem to be more than 10 times harsh than the previous. When I tried to calculate level of oppression committed together by the military government and EPRDF, it is to be 14 times higher today than it has been in the past; the time of the monarchy. We, therefore, need to bring remedy to heal the Ethiopian people that are suffering 14 times much more badly than the previous times.
Admittedly, it is peaceful struggle, an important and vital way to overthrow the ethnic affiliated TPLF government. Peaceful struggle is a remarkable way which after all protects the people from deceasing without meaning. However TPLF, the entity without principle, (born in the bushes), its undemocratic nature will not allow it accept a peaceful and civilized manner of peaceful transition. TPLF used its military mighty, not to willingly submit power to the first publicly elected party in Africa; Coalition for Unity and Democracy (CUD or KINIJIT). It is the spirit of this CUD which is carrying the rifle. The reason of-course is to take back the stolen people power from TPLF. Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracy (PG7) which is garbing the spirit of CUD do not in principle prefer armed struggle and blood shade. War is not at all its values. PG7 has carried the principles of love than hatred. PG7 has no hostile organizations or persons. The peaceful hands of PG7 will never bended.
PG7 does not engage in non-sense quarrels, pointless disagreements and verbal conflicts. In contrast it consumes its energy to bring order. PG7 marched along the road of love and harmony to wipe off illusions and all the gloomy ideas from the minds of existing Political Parties and the people. The main objective of PG7 is to clear the sky of the country from the dark cloud that was covered by past undemocratic methods of right wing (communist) hostile political thoughts. I am a young man which does not know all about the past history of Ethiopian politics. But as member of PG7, I learned many essential ideas. After all I learned that genuine politics is an outcome of concordance (order) and harmony. People always support politics based on harmony.
Those patriotic fronts that have headquarters in Eritrea do not get any material support from Eritrean regime. The only agreement, that can be speculated, between the patriotic fronts and the Eritrean regime, would be, using the land of Eritrea as base and headquarters. Dr. Birhanu Nega, chairman PG7 front, has repeatedly informed the reality of this fact. PG7 believes that the suspicion may emerge from genuine feelings of some people that are preoccupied to know what is going on. Anyway any illusion will be cleared by agreements and discussions.
There is one fact. The ruthless dictator TPLF is solitary. That is why its leaders chose war. In any form they prefer war because they left with no other options. Of-course war is like playing with fire. TPLF is not capable of conducting war, or cannot even walk an inch. Corruption corrupts its entire entity. TPLF went to its birth place, the cave of Dedebit, to honor its 40th years of birthday after knowing that celebration is the only business left ahead. TPLF however realized that the cave is no more a hiding place. The caves have already begun to cooperate with the Ethiopian people. They (the caves) are sorry for the role they played as shelter to the TPLF in the past.
If war between the Patriotic Fronts and TPLF break out, the TPLF surely knows that the people of Ethiopia will never stand by its side. Too many people of different races and genders at Kaliti, Kilinto and Zwai prisons are suffering. Atrocities and racial differences are enormous. This is the reality. It would then be ignorance if TPLF believes that the people will support its rule. Even the Armed Forces and the Federal Police Force are not in good shape to support TPLF. PG7 respects the continued existence of the Ethiopian Armed Forces and the Federal Police. Even after the ruling TPLF is overthrown the defense forces will not be disbanded as was intentionally committed in revenge by TPLF 24 years ago.
PG7 is medicament. PG7 is love, harmony and peaceful way to democracy and the ballot box. Hence, the people will begin to administer themselves through the elected representatives. PG7 envision the creation of peace and will pay the necessary sacrifice to achieve this goal. PG7 has no enemy but the political system of TPLF. PG7 will fight against the system and not humans. PG7 do not believe in apprehending persons and throw into prisons. PG7 is medicament.
Victory to the Ethiopian People
G. M.