ኦነግ - ፊንፊኔ ብሎ አውጆ ሥልጣን ከመያዙ በፊት ሥራ ላይ እያዋለ ያለው ቀዳሚው ስልት ወይም የሥራ ልምምድ "ተረኝነት" ይባላል። "አማራ ሶስት ሺህ ዓመት ገዝቷል፣ ትግሬ ሃያ ስምንት ዓመት ገዝቷል፣ ተራው የእኛ ነው" የሚለው የተረኝነት ቦለቲካ ከየት እንደመጣ አይታወቅም። ግን መሬትን በመቸብቸብ፣ ገንዘብ በመዝረፍ፣ ሥልጣን ካለችሎታ በመያዝ - የሚተገበረው ተረኝነት ለነገ የሚቀመጥ አበሳ ነው። በኃይለሥላሴ ዘመን እኮ ሥልጣን በትምህርት ችሎታ ነበር የሚለካው። በደርግ ዘመን የነበሩት እውቅ የኦሮሞ ልጆች ከፍተኛ ቦታ የያዙት በእውቀታቸው ነበር። በንጉሡም በደርግም ዘመን ቁልፍ ቦታ ላይ የነበሩት የኦሮሞ ምሁራን ለዕይታ እኮ አልነበረም ወንበሩን የያዙት በእምቅ ችሎታቸውን አስተዳደርን ሊተገብሯት እንጂ።
No comments:
Post a Comment