Saturday, March 26, 2016

ፍትህ በ ወያኔ ዘመን
ፍትህ (justice)፣ በኢትዮጵያ ፍትህ ደብዝዛለች። ደብዳቢውና ተደብዳቢው ፖሊስ ጣብያ ቢሄዱ ተደብዳቢው ይታሠራል። ዘራፊና ተዘራፊ ሸንጎ ፊት ቢቀርቡ ተዘራፊው ተሸማቆ ከእልፍኙ በአፋጣኝ እንዲወጣ ይደረጋል። ዳኛና ጠበቃ የጥቅም ትሥሥር አድርገዋል። ፍርደ ገምድል ዳኛው የባለጉዳዩን ሳይሆን የጠበቃውን እጆች ያያል። ደህና ጉቦ ሰጪ ጠበቃ ዝናን ያተርፋል፣ በርካታ ደንበኞች ያፈራል። ለፍትህ የቆሙ ጠበቆች ደግሞ ሥራ ፈተዋል። "ፍትህ ይስፈን" እያሉ ሲጮኹ ሙሰኛው ዳኛና መሠሪው ጠበቃ ይሳለቁባቸዋል። ፍትህ በኢትዮጵያ እጅግ ተረግጣለች። ታድያ በአቋራጭ ለመክበር ኢፍትሃዊ ነገሮችን ሳይፈሩ መፈጸም እየተለመደ መጥቷል። በኢፍትሃዊ አሠራሮች ልምድን የቀሰሙት ደላሎችና አቀባባዮች የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ። እነርሱ ለዳኞችና ጠበቆች ሐሰትን አደልቦ እንደምን ማሸነፍ እንደሚቻል ህግን ሳይፈሩ፣ ሰውን ሳያፍሩ ምክር ያካፍሏሉ። ክፉዎች የምክር አገልግሎት በሚሰጡባቸው ቢሯቸው ውስጥ የፍትሃብሄር ህግና መጽሃፍ ቅዱስ ሁለቱም ጠረቤዛው ላይ ተቀምጠዋል። አይ ዘመን!

Friday, March 25, 2016

ሰበር ዜና
ዶክተር መረራ ጉዲና ከሀገር እንዳይወጡ ተደረገ። ወደ አሜሪካ ለመምጣት ትላንት ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ቢሄዱም መውጣት አልቻሉም። ዛሬ ወደ ኢሚግሬሽን ሄደው ሃላፊው ስብሰባ ገብተዋል ተብለው ተመልሰዋል። 
''ፓስፖርትዎን መሳሪያው ማንበብ አልቻለም። ምናልባት ሽቶ ነክቶት፡ ወይም ዘይት ተደፍቶበት ሊሆን ይችላል።'' 
ቦሌ የኢሚግሬሽን(ደህንነት) አንድ ሰራተኛ የተናገረው

Monday, March 21, 2016

የወልቃይት ጠገዴ ዳንሻህ ህዝብ በአሁኑ ሰዓት በወያኔ ጦር ጥቃት እየተሰነዘረበት የዘር ማጥራት እየተካሄደበት ነው

የወልቃይት ጠገዴ ዳንሻህ ህዝብ በአሁኑ ሰዓት በወያኔ ጦር ጥቃት እየተሰነዘረበት የዘር ማጥራት እየተካሄደበት ነው
ሰበር ዜና
በዳንሻ ግጭት ተፈጥሯል። በትግራይ ልዩ ፖሊስና በወልቃይቶች መሀል የተኩስ ልውውጥ ተደርጓል። መንገዶች ተዘግተዋል። በአቅራቢያ ባሉ መንደሮች የሚገኙ የወልቃይት ነዋሪዎች ተቃውሞ እያሰሙ ነው።

Saturday, March 19, 2016

ሕወሓት እና የመሬት ቅርምቱ

ሕወሓት እና የመሬት ቅርምቱ
መሬት (Land)፣ መሬት በሕዝባዊ መንግሥት ቁጥጥር ሥር ስትውል ልማት ባግባቡ ይፋጠናል። በሃገራችን የመሬት ጉዳይ የፍትህ ጉዳይ አልፋና ኦሜጋ ነው። የተፈጥሮ ኃብት (Natural resources) ከጉልበትና ዓዕምሮ (labour and mental) ጋር ሲዋሃድ ምርትን (production) ያስገኛል። መሬት የተፈጥሮ ኃብት ዋነኛ መፍለቅያ ምንጭ ነች። ማንም ሠላምንና ጸጥታን፣ ልማትንና እድገትን የሚፈልግ ስብስብ የመሬትን ጉዳይ ፍትሃዊ (justify) ለማድረግ ሲል ጠቃሚ መሠረታዊ ህጎችን (system of rules)በቅጡ ይቀርጻል። ይህ ጉዳይ ፈጽሞ ተግባራዊ መሆን ካልቻለ ጥቁር ገበያዎች (black markets) እንደ አሸን ይፈላሉ። ጥቁር ገበያ በሙስና (Corruption) የሚመራ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ፍዳና ዕዳ ነው። መሬት የመንግሥት ኃብት እንዲሆን ፈላስፎችና የምጣኔ ኃብታዊ ሊቆች እጅግ ሠፊ ሳይንሳዊ ትንታኔ ሠጥተዋል። "መሬት ላራሹ" በኢትዮጵያ ተራማጆች ዙርያ ዘወትር ሲነሳ የቆየ ታሪካዊ መፈክር ነበር። የተጨቋኖችና አጋሮቻቸው እምቅ አስተሳሰብ የወለደው ይህ ታሪካዊ መፈክር ተንቆ ይባስኑ የኢቶዮጽያ መሬት የቀማኞችና ሙሰኞች መገልገያ ሆኗል። በኢቶዮጽያ መሬት አሞሌ ጨው ተሸክሞ ለመጣ ሁሉ በቀላሉ እንደምትቸረቸር ኮማሪት ተንቃለች። መሬት "በሶስተኛ ደላሎች" ስም እንደዋዛ የምትለወጥ ጉቦኛ ባለሥልጣናትና መዝባሪው ነጋዴ የሚሻሟት አሳዳሪ የራቃት ባለቤት አልባ ሆናለች። መሬት በኢቶዮጽያ ምን ያልሆነችው አለ? አሜሪካ የተፈጠረችው በቀይ ሕንዶች ደም ላይ ነው። አሜሪካ የተገነባችው በአፍሪካውያን ባርያዎች ግፍና ሰቆቃ ነው። ይህን ግፍ የዲሞክራሲ ቋሚ ምሰሶ ወይም ዓምድ አይደለም። ገዥው መንግሥት ሰዎችን በፌደራል ፖሊስ ጥይት ካስገደለ በኋላ "ለዲሞክራሲው ግንባታ ገና ነን፤ አሜሪካ እስከ ስድሳዎቹ መባቻ ድረስ ሰዎች ይገደሉ ነበር" ብሎ ያወራል። አገዛዙ ልማቱን እየዘረፈ፣ ሰዎችን እንደ ቀይ ሕንዶች ከቀዪአቸው እያፈናቀለ፣ ጥሬ ሃብቱን ለባዕድ እየቸረቸረና "መሬቴን አትንኩ" ያሉትን ነዋሪዎች እያሽመደመደ "ዲሞክራሲው ገና አልጎለበትም" ብሎ ያሾፋል። ይህን ትምህርት የቀሰሙት ከሱዛብን ራይስ ከሆነ ያሳዝናል። መልካሞቹን የዲሞክራሲ እሴቶችና የመልካም አስተዳደር መርህን ካደጉት ሃገሮች ተሞክሮ እየቀሰሙ ማዳበር ሲቻል መሬትን ለመቀራመት ብሎ ተወላጁን፣ አገር በቀሉን (indigenous) መግደል የዲሞክራሲ ባህሉም ወጉም አይደለም።

Thursday, March 17, 2016

ኦሮምያና “ልማታዊ ሙስናዎቿ”

ኦሮምያና “ልማታዊ ሙስናዎቿ”

ኦሮምያና "ልማታዊ ሙስናዎቿ"ከሚክያስ ግዛው (visit my blog  http://michyas.blogspot.no/ )
እኔ እንኳን ወያኔ በፈጠራቸው ዘረኛ የክልል ስሞች አካባቢዎችን መጥራት አልፈልግም ነበር። በዘር፣ ነገድ፣ ጎሳና ጎጥ የሚወሰን የማንነት ግንባታ (identity empowerment) አፍራሽ ይመስለኛል። ብቻ ይሁን እስቲ ወለጋ፣ አርሲ፣ ሐረርጌ፣ ባሌ፣ ወዘተ ማለቱን ትቼ እንደው እንደዘበት "ኦሮምያልበል። ኦሮምያ ውስጥ ሙስና (corruption) እንደ አንድ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ዘርፍ (political economic sector) ተቆጥሮ ዋልጌዎች ሳይፈሩና ሳይሸማቀቁ እየተገበሩት ይገኛሉ። ይህ በደጋግና ጀግኖች ሕብረተሰብ ማህል የተደነቀረው የክፋት ገጽታ የመልካም አስተዳደር መርሆችን (good governance principles)፣ ባህላዊ ትሥሥሮችንና ሥነ-ምግባርን በማጨለሙ ሕዝቡን ለድህነት ዳርጓል። እስቲ እኔ ከታዘብኩት ውስጥ ጥቂቱን ላካፍላችሁ።
እውነት (Truth)፣ እውነት እምነት ነች። ሰዎች ስለአካባቢያቸውም ሆነ የዓለም ዙርያ እንቅስቃሴና ክንውኖች እውነቱን የማወቅ መብት አላቸው። ሰዎች እውነትን ሲረዱ ወደፊት ሊተገብሩ ስላቀዱት ዓላማ ግንዛቤ ይጨብጣሉ። በኦሮምያ የስልጣኑ ባሌቤት ኦሕዴድ ቀድሞውም ቢሆን በእብለት መሠረት ላይ የታነጸ በመሆኑ እውነት ማንጸባረቅ አይችልም። ድርጅቱ ባለቀልም የዋርካ ሥዕል ያለበት ባንዲራ እያውለበለበ ወደ ስብሰባ አዳራሽ ከመንጎድ ውጭ ፋይዳው አይታይም። በአሮምያ ክንውኖች ሁሉ ህፀፅዊ(fallacious) ወደ መሆን ደርሰዋል። በየስብሰባው ውሃ የመይቋጥሩ አረፍተሃሳቦች (fallacious arguments) ይወረወራሉ። ባለስልጣናት ሕዝቡን በመናቅ አደናጋሪና አሳሳች (deceptive, misleading ; fallacious testimony) መረጃዎችን ይበትናሉ። የውስጡ መሠረታዊ ችግር ሳይመረመር ላይ ላዩን የተድበሰበሰ (disappointing; delusive) መፍትሄ መሰል ሃሳብ ቀርቦ ስብሰባው በተዳፈነ ሠላም (fallacious peace) ይጠናቀቃል። በእርግጥ ሁሉንም በአንድ ላይ መጨፍለቅ (generalization) ተገቢ አይደለም። የለበሱትን ሕዝባዊ አደራ በንፃት የሚጠብቁ ቢኖሩም የሙሰኞቹ ጥቁር ሥራ ግን በጎ ክንውኖችን ማጉደፉ አልቀረም። እውነት ኦሮምያ ምድር ሞታ ልትቀበር ትንሽ ቀርቷታል።
መሬት (Land)፣ መሬት በሕዝባዊ መንግሥት ቁጥጥር ሥር ስትውል ልማት ባግባቡ ይፋጠናል። በሃገራችን የመሬት ጉዳይ የፍትህ ጉዳይ አልፋና ኦሜጋ ነው። የተፈጥሮ ኃብት (Natural resources) ከጉልበትና ዓዕምሮ (labour and mental) ጋር ሲዋሃድ ምርትን (production) ያስገኛል። መሬት የተፈጥሮ ኃብት ዋነኛ መፍለቅያ ምንጭ ነች። ማንም ሠላምንና ጸጥታን፣ ልማትንና እድገትን የሚፈልግ ስብስብ የመሬትን ጉዳይ ፍትሃዊ (justify) ለማድረግ ሲል ጠቃሚ መሠረታዊ ህጎችን (system of rules)በቅጡ ይቀርጻል። ይህ ጉዳይ ፈጽሞ ተግባራዊ መሆን ካልቻለ ጥቁር ገበያዎች (black markets) እንደ አሸን ይፈላሉ። ጥቁር ገበያ በሙስና (Corruption) የሚመራ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ፍዳና ዕዳ ነው። መሬት የመንግሥት ኃብት እንዲሆን ፈላስፎችና የምጣኔ ኃብታዊ ሊቆች እጅግ ሠፊ ሳይንሳዊ ትንታኔ ሠጥተዋል። "መሬት ላራሹበኢትዮጵያ ተራማጆች ዙርያ ዘወትር ሲነሳ የቆየ ታሪካዊ መፈክር ነበር። የተጨቋኖችና አጋሮቻቸው እምቅ አስተሳሰብ የወለደው ይህ ታሪካዊ መፈክር ተንቆ ይባስኑ የኦሮምያ መሬት የቀማኞችና ሙሰኞች መገልገያ ሆኗል። በኦሮምያ መሬት አሞሌ ጨው ተሸክሞ ለመጣ ሁሉ በቀላሉ እንደምትቸረቸር ኮማሪት ተንቃለች። መሬት "በሶስተኛ ደላሎችስም እንደዋዛ የምትለወጥ ጉቦኛ ባለሥልጣናትና መዝባሪው ነጋዴ የሚሻሟት አሳዳሪ የራቃት ባለቤት አልባ ሆናለች። መሬት በኦሮምያ ምን ያልሆነችው አለአሜሪካ የተፈጠረችው በቀይ ሕንዶች ደም ላይ ነው። አሜሪካ የተገነባችው በአፍሪካውያን ባርያዎች ግፍና ሰቆቃ ነው። ይህን ግፍ የዲሞክራሲ ቋሚ ምሰሶ ወይም ዓምድ አይደለም። ገዥው መንግሥት ሰዎችን በፌደራል ፖሊስ ጥይት ካስገደለ በኋላ "ለዲሞክራሲው ግንባታ ገና ነን፤ አሜሪካ እስከ ስድሳዎቹ መባቻ ድረስ ሰዎች ይገደሉ ነበርብሎ ያወራል። አገዛዙ ልማቱን እየዘረፈ፣ ሰዎችን እንደ ቀይ ሕንዶች ከቀዪአቸው እያፈናቀለ፣ ጥሬ ሃብቱን ለባዕድ እየቸረቸረና "መሬቴን አትንኩያሉትን ነዋሪዎች እያሽመደመደ "ዲሞክራሲው ገና አልጎለበትምብሎ ያሾፋል። ይህን ትምህርት የቀሰሙት ከሱዛብን ራይስ ከሆነ ያሳዝናል። መልካሞቹን የዲሞክራሲ እሴቶችና የመልካም አስተዳደር መርህን ካደጉት ሃገሮች ተሞክሮ እየቀሰሙ ማዳበር ሲቻል መሬትን ለመቀራመት ብሎ ተወላጁን፣ አገር በቀሉን (indigenous) መግደል የዲሞክራሲ ባህሉም ወጉም አይደለም።
ኢንቨስትሜንት፣ (investment) እኔ ራሴ investment, establishment, department, እንደው ምናለፋችሁ «ment» ያለበት እንግሊዘኛ ሲነገር እፈራ ነበር። ግናስ የሠፈራችን አንድ አጉራ ዘለል "ኢንቬስተርተብሎ ከውጭ ሲመጣ ቃሉን ተለማመድኩኝ። ምን ሊቨሰትር ነውብዬ ስጠብቅ አቀባባይ ረድፈኞችን በእንግሊዘኛ ደልሎ አስደልሎ መሬት ጨመደደ። መሬቱን ደግሞ ሸጦ ገንዘቡን መሬቱን ከሰጡት ከባለስልጣናት ጋር ተካፈላው ሲባል ሰማሁ። በኦሮምያ ብዙ ኢንቬስተሮች ይስተናገዳሉ። ከባለሱቁ አንስቶ እስከትላልቅ ሳሙና፣ ዘይትና ብስኩት ፋብሪካ ድረስ በሙስናው ማህደር ተመዝግቦ በጉቦኛው ማህተም ይለፍ የተመታለት የንግድ ተቋም ሁሉ "እንቬስትሜንትተብሎ ይወደሳል። ባንዳንድ አካባቢዎች የኢንቬስትሜንቱ ባለቤቶች (clandestine wealth) "የማይታዩት ባለስልጣኖችወይንም ተባባሪዎቻቸው ሲሆኑ የንግድ ፈቃዱ የተመዘገበው ባንድ ጭቁን የኢንቬስተሩ ሎሌ ነው። ይህ ዘመናዊ የሎሌነት ሥራ የተቀዳው በቅኝ ግዛት ሥር ከነበሩት የአፍሪካ ሃገሮች ነው።
ስብሰባ (session)፣ አስተማሪያችን "ስብሰባ ሎጂክ (logic) መጠቀምያ ጠቃሚ ጊዜ ነውሲሉ እሰማ ነበር። የፍርድ ሸንጎ ሠብሳቢ የነበረው አጎቴ ደግሞ "የስብሰባ አዳራሽ ዝም ብሎ ተሰባስቦ እንቅልፍና ራስ ምታት መሸመችያ ቦታ አይደለምይል ነበር። ሰው ከተሰበሰበ ንድፈ ሃሳብ አፍልቆ፣ እልባት ያለው ውሳኔ ሸክኖ ለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ አለበት (Theory + practice = Praxis)። ኦሮምያ ስብሰባ ታበዛለች። በሃያ አምስት ዓመታት ኦሮምያ ያስተናገደችው ስብሰባ በሜትር ሲለካ የዓለም ሊግና የተባበሩት የዓለም መንግሥታት ማህበር ካደረጉት ስብሰባ በሶስት እጥፍ ይበልጣል። ምን ንድፈ ሃሳብ ተወረወረምን ተወሰነምን ተፈየደምንም። በእርግጥ እድሜ ለሙስና ሠማይ ጠቅስ ሕንጻዎች ቆመዋል፣ ጥሬ ኃብቱንና ምርቱን ማጓጓዣ ይሆን ዘንድ መንግሥት ዘመናዊ መንገድ አንጥፏል። የሕዝቡ ኑሮ ግን አልተሻሻለም። የሕዝቡ ባህልና እሴቶች ተደፍጥጠዋል። ተሰብሳቢዎች የሙስናንና ጉቦ መርሆችን በሰምና (wax) ወርቅ (gold) አሽሞንሙነው ይለያያሉ። ሰሙ "ሙስና ይጥፋሲሆን ወርቁ ደግሞ"ሙስና እጥፍ ይሁንነው። የመናገር ችሎታ፣ በእጅ የመሄድ አክሮባትና ድፍረት መለማመጃ የሆነው የኦሮምያው ሙስና ወለድ ስብሰባ ብዙ ገንዘቦች አባካኝ ጎጂ ባህል እየሆነ መጥቷል። ሃቀኛ ነጋዴዎች የመንግሥት ገቢ ለመክፈል ማለዳ ወደ አገር ውስጥ ገቢ ሲሄዱ "ፋይሉ አልተገኘምተብለው በኪራይ ሰብሳቢዎች ይባረራሉ። ችግሩን ለማን አቤት ይባላል። አለቆች ስብሰባ ላይ ናቸው። ሃቀኞች ዓመታዊውን ግብርና መንግሥት የደነገገውን ቫት ለመክፈል እንኳን ተቸግረዋል። የመንግሥትን ገቢ ለማስገባት ሙስና ለምን አስፈለገፋይሉ ጠፍቷል በመባሉ ምክንያት ግብር የተቆለለበት ሃቀኛ ነጋዴ ሲጉላላ ማየቱ አሳዛኝ ነው። ይህ ክፋት ኬንያና ናይጄርያም እንኳን አልተከሰተም። በኦሮምያ "ስብሰባሙስናን ማጠናከርያና ኪራይ ሰብሳቢዎችን ማሰልጠኛ ሠንበቴ ከሆነች ሰነበተች።
ፍትህ (justice)፣ በኦሮምያ ፍትህ ደብዝዛለች። ደብዳቢውና ተደብዳቢው ፖሊስ ጣብያ ቢሄዱ ተደብዳቢው ይታሠራል። ዘራፊና ተዘራፊ ሸንጎ ፊት ቢቀርቡ ተዘራፊው ተሸማቆ ከእልፍኙ በአፋጣኝ እንዲወጣ ይደረጋል። ዳኛና ጠበቃ የጥቅም ትሥሥር አድርገዋል። ፍርደ ገምድል ዳኛው የባለጉዳዩን ሳይሆን የጠበቃውን እጆች ያያል። ደህና ጉቦ ሰጪ ጠበቃ ዝናን ያተርፋል፣ በርካታ ደንበኞች ያፈራል። ለፍትህ የቆሙ ጠበቆች ደግሞ ሥራ ፈተዋል። "ፍትህ ይስፈንእያሉ ሲጮኹ ሙሰኛው ዳኛና መሠሪው ጠበቃ ይሳለቁባቸዋል። ፍትህ በኦሮምያ እጅግ ተረግጣለች። ታድያ በአቋራጭ ለመክበር ኢፍትሃዊ ነገሮችን ሳይፈሩ መፈጸም እየተለመደ መጥቷል። በኢፍትሃዊ አሠራሮች ልምድን የቀሰሙት ደላሎችና አቀባባዮች የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ። እነርሱ ለዳኞችና ጠበቆች ሐሰትን አደልቦ እንደምን ማሸነፍ እንደሚቻል ህግን ሳይፈሩ፣ ሰውን ሳያፍሩ ምክር ያካፍሏሉ። ክፉዎች የምክር አገልግሎት በሚሰጡባቸው ቢሯቸው ውስጥ የፍትሃብሄር ህግና መጽሃፍ ቅዱስ ሁለቱም ጠረቤዛው ላይ ተቀምጠዋል። እግርግዳው ላይ ደግሞ "እግዚአብሄር ያያልየሚል በእንግሊዘኛና ኦሮምኛ የተጻፈ ጥቅስ ተሰቅሏል። አይ ዘመን!
አቀባባይ ረድፈኛ ሚና (liaison role between the corruptor and corruptors of public officials) አቀባባይ ረድፈኛ (እንደ ራሴ አተረጓጎምበሙያው ደላላ ያልሆነ ስልታዊ ደላላ ነው። ከደላሎች የሚለየው ነገር ቢኖር ባለስልጣኖችን በጥቅም አሳውሮ መቅረብ መቻሉ ነው (dangerous liaison)። የመናገርና የማሳመን ፣ የማዘበራረቅና የማዛባት ችሎታ የተላበሱት አቀባባይ ረድፈኞች አገዛዙ ባመቻቸው የሙስና መሠላሎች ወደ ላይ የወጡ የዘመኑ አራዶች ናቸው። እነዚህ አቀባባይ ረድፈኞች ጉቦ ሰጪንና ጉበኛን፣ ሠነፍ ተማሪንና ቦዘኔ አስተማሪን፣ ባለስልጣንንና አራጣ አበዳሪውን፣ ፍርደገምድል ዳኛውንና ቆቁን ጠበቃ፣ ወዘተ፣ አገናኝ ናቸው። ካለነዚህ አቀባባይ ረድፈኞች እገዛ ውጭ ባለስልጣን ሊመዘብርና ሙስና ሊቀበል ያዳግተዋል። መሥሪያ ቤቶችን ሁሉ የሙስናና ምዝበራ አርማ ተሸካሚ ያደረጉት እነዚህ በስልታዊ ብረዛ ሳይንስ የተካኑት አቀባባይ ረድፈኞች ዋዛ አይደሉም። ህግና ፍትህ ሚኒስቴር – ሙስናና አድልዎ ሚኒስቴር፣ የንግድ ሚኒስቴር – የምዝበራ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር – መሃይምነት ማስፋፍያ ሚኒስቴር፣ መከላከያ ሚኒስቴር የጨረታና መሬት ሽሚያ ሚኒስቴር፣ የገንዘብ ሚኒስቴር – የዋጋ ንረት ሚኒስቴር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር – ኢንቬስትሜንትና ሃዋላ ሚኒስቴር፣ የእርሻ ሚኒስቴር – እንጀራና በርበሬ ላኪ ሚኒስቴር፣ ወዘተ፣ እንዲሆን ሚናውን የተጫወቱት መለኞች ከአስመጭና ላኪዎቹ ወይም ሕንጻ አከራዮቹ ባለስልጣኖች ቢሮ ላፍታም ቢሆን የማይርቁ የሙስናና ዝርፍያው ተቋም (kleptocracy) ባለውለታዎች ናቸው።
ቋንቋ (mother tongue)፣ በኦሮምያ ኦሮሚፋ ብቻ ነው የሥራ ቋንቋ። ልጆቿ ሌላ ክልል ሄደው መሥራት አይችሉም። እሷም ከትግራይ ወይም አማራ አልያም ጋምቤላ፣ አፋር፣ ሶማሌ ወይም ደቡብ ክልሎች የሚመጡትን ልጆች አታስተናግድም። አትድረሱብኝ – አልደርስባችሁም ብላለች። ኦሮምያ አማርኛ ቋንቋን እንደ መጨቀኞ መሣርያ ያህል በመጥላትዋ ሳብያ አፈሯን ፈጭተው፣ ውሃዋን ጠጥተው ያደጉትን ኦሮምኛ የማይችሉትን አንጡራ ልጆቿን እንኳን የጉዲፈቻ ዜግነት ከልክላቸዋለች። ኦሮምያ አማርኛ የነፍጠኞች ቋንቋ መሰላት እንጂ የጋራ መግቢያብያ ቋንቋ ልማትን እንደሚያፋጥን ቴክኖሎጂንም እንደሚያስፋፋ አላጤነችም። አማርኛ የመንግሥት የሥራ ቋንቋ ሆኖ ለብዙ ዓመት ማገልገሉ ማንንም ባልጎዳ ነበር። የሆነስ ሆነና የኢትዮጵያ ሁለተኛ የሥራ ቋንቋ እንግሊዘኛ መሆኑስ ይታወቃልኦሮምያ ይህን የልማት እንቅፋት ሽራ ይልቅስ ብዝህነትን በማስተናገድ የኢትዮጵያ አንድነትን ማጠናከር ቀዳሚ ሚናዋ ሊሆን ይገባል።
ባጠቅላይ ሃቀኝነት፣ ደግነት፣ ፍትሃዊነት፣ ሙስናንና ጉቦን መጸየፍ – እነዚህ የሕዝቡ የመልካም ባህርይ መገለጫ የሆኑት እሴቶች በኦሮምያ ውስጥ ወደ ጉሮኖ ተወርውረዋል። እነዚህን እሴቶች ዳግም ሊያንጸባርቅ የሞከረ ሁሉ መሳለቅያ ይሆናል። ኬንያና ናይጄርያ በሙስናና ጉቦ ጫፍ ላይ የደረሱ ሃገሮች እየተባሉ ሲነገር ቆይቷል። ኦሮምያ ደግሞ በጥቂት ዓመታት ክብረወሰኑን አልፋ የሙስናና ጉቦ ፍልስፍና የተሃድሶ ምድር እንዳትሆን ያሰጋል። ይህን የመሳሰሉት ግፎች ናቸው ዛሬ ሕዝቡን ለአመጽ ያነሳሱት። የፍትህ መዛባት፣ እስር፣ ግድያና የምጣኔ ኃብቱ ይዞታ ልዩነት ካልተገደቡ በቀር ሕዝቡን ለመብቱ ከመታገል የሚያቆመው አንዳች ኃይል የለም። የፌደራል መንግሥቱ እጆች "አመድ አፋሽወይም የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ እንዳሉት"የኢትዮጵያ ሕዝብ ወርቅ ቢያነጥፉለት..."ሆኖ አይደለም ይህ ሁሉ አመጽ የበረከተው። ሙስናው፣ የአስተዳደር በደሉ ኑሮውን አናግተውበት በድህነትና ሰቆቃ ጅራፍ መገረፉ፣ በአምባገነኖች (tyranny, timocracy, oligarchy, plutocracy) ውሳኔ ብቻ መነዳቱ አልበቃ ብሎ ቀማኞች መሬቱንና የመሬቱን የተፈጥሮ ገጸበረከት በጠመንጃ አስገድደው (military command) በጠራራ ፀሃይ ስለሚዘርፉት እንጂ። የእርምቱ እርምጃ ከሰላው ጫፍ ይጀመር።
ጥቂቶቹ የትግራይ ሕወሓት መሪዎች ለም የሆኑትን የጎንደርና ወሎ አጎራባች መሬቶች በማናለብኝነት ተነሳስተው ወደ ትግራይ ክልል መደባለቃቸው ያስከተለውን አደጋና የህዝብ ቁጣ በሚቀጥለው ጊዜ እዘግባለሁ።
እግዚአብሄር ቸር ዘመን ያምጣልን፣ አሜን

Tuesday, March 15, 2016

ሲኖ ትራክ (Sino Truck) ሲኖ ጭራቅ፣ ቀይ ሽብር – ከ ሚኪያስ ግዛው 

ሲኖ ትራክ (Sino Truck) ሲኖ ጭራቅ፣ ቀይ ሽብር – ከ ሚኪያስ ግዛው 

እነዚያ ቀያዮቹን የቻይኖች መኪኖች ገና ከሩቅ ሲያዩ ጭራቅ የመጣባቸው ያህል ልጆች ይርበደበዳሉ። ገና የሲኖ ትራኩን ድምጽ ሲሰሙ የከለላና መከታ አያያዝ ስልትን ያልተማሩት እነዚያ ጨቅሎች የሚደበቁበትን ቦታ ለመምረጥ ሲባዝኑ ይታያሉ። "ሲኖ ትራክን ገና ከሩቁ ስታዩ..." እያሉ ወላጆቻቸው ጠዋት ጠዋት የሚነግሯቸው የጥንቃቄ አወሳሰድ ምክር ትምህርቱን አስረስቷቸዋል። ይህንኑ አደገኛ ቀይ መኪና ወላጆች በዘመናቸው ካዩት ዘግናኝ ድርጊት ጋር በማመሳሰል "ቀይ ሽብርብለውታል።
ሃገራችን ኢትዮጵያን አንገቷን ካስደፋት ትላልቆቹ ክፋቶች መካከል የመልካም አስተዳደር እጦት፣ ስግብግብነትና የኅሊና መሸርሸሩ እጅግ አሳዛኞቹ ናቸው። ሃገር የቱንም ያህል ለማች፣ በሰማይ ጥቀስ ሕንጻዎች አሸበረቀችም ሆነ ዘመናዊ መንገዶች ተነጠፉላት ሥነ-ምግባርና ግብረገብነት ከተሸረሸሩ "ውሃ ቢወቅጡት እምቦጭነው።
በንጉሡም ይሁን በደርግ ዘመን ሙስናና ጉቦ ቢኖርም እንዲህ እንዳሁን ሕዝቡን አላንገሸገሸም ነበር። አብዛኛው ሰው ፈሪሃ እግዚአብሄርነት በውስጡ ስላደረ በኅሊናው ይተዳደር ነበር። በደርግ ዘመን "መንጃ ፍቃድ በጉቦ አውጣ"፣ "መንጃ ፈቃድ ቤቱ ድረስ መጣለት"፣ ሲባል ሰው ወሬውን እንደ ጉድ ተገረሞ ያዳምጥ ነበር። ሰውንም ራስንም አደጋ ውስጥ የሚከት መርዝን በጉቦ መሸጥ የቴክንሽያኑን ኅሊና ቢስነት ደረጃ መገመቻ ነበር። መንጃ ፈቃድ በጉቦ መስጠት የሞት ፍርድ ያህል ነበር። ዛሬ እፍረት መሆኑ ቀርቶ ሁሉም ነገር ሙስናና ጉቦ ሆኗል። ሙስና ሞትንም ትሸጣለች። መሬት በጉቦ ይቸረቸራል። ባለገንዘብ መሬት ገዝቶ ጭሰኞች ይቀጥራል። የሠማይ ስባሪን ያህል ሹመት ተሸካሚ ግለሠብ ሕንጻ አከራይ ሁኗል። የሕዝብ አደራ የተሸከመው አገልጋይ አስመጭና ላኪ ነጋዴ ሆኗል። አለማየሁ እሼቴ ምናልባት በስድሳዎቹ መግቢያ ላይ ነው መሰለኝ፣ ባማረ ድምጹ - "ማን ይሁን ትልቅ ሰው" - በሚለው ዘፈኑ ላይ - "እባክህ አምላኬ ደጉን ዘመን አምጣ" - ሲል ለእግዚአብሄር ምልጃውን አቅርቦ ነበር። የየኔውን ዘመን ገምቶ አምላኩን የተማጸነው ከያኒ ዛሬስ ምን ታዝቧልምናልባት አለማየሁ እሼቴ እንደገና ቢያንጎራጉር "እባክህ አምላኬ ያን ዘመን መልሰውይል ይሆንበእርግጥ የዘንድሮው ከተሻለ ያምናው ታሪክ ነበር። አለመታደል ሆኖ እንጂ "ከዘመን ዘመን አሸጋግረንማለት ከኋለኛው ዘመን ወደ አዲሱ ዘመን በላቀ መንፈሳዊ ጽናት፣ በተሻለ ሠላምና ብልጽግና አሸጋግረን ማለት ነው። "ልማታዊው መንግሥትሥነ-ምግባሩንና ግብረገብነቱን ሸርሽሮ ሁሉንም ደረመሰው።
ሲኖ ትራክ ምንም አላጠፋም። ሲኖ ትራክ በቻይና የተፈረበከ ፈጣን ጉልበታማ መኪና ነው። ጥፋቱ የሹፌሩ ነው። ጥፋቱ የአሽከርካሪው ነው። በእርግጥ ጥፋቱ የአሽከርካሪው አይደለም። ጥፋቱ የሥርዓቱ ነው። ጥፋቱ በእድሜው ለጋ ለሆነው ወጣት ወይም ሱሰኛ ካለችሎታው አራተኛና አምስተኛ ደረጃ መንጃ ፈቃድ የሚሰጠው የየክልሉ መሥሪያ ቤት ነው። ቀድሞ መንጃ ፈቃድ በትምህርት ዲግሬ ከማግኘት ያላነሰ ፈተናና ውጣ ውረድ ነበረው። ቀድሞ መንጃ ፈቃድ ለማግኘት ከሁለተኛ ደረጃ ወደ ሶስተኛ፣ ከሶስተኛ ወደ አራተኛ፣ ከአራተኛ ወደ አምስተኛ፣ ለመዝለል እጅግ ከፍተኛ ልምድንና ብስለትን ይጠይቅ ነበር። ዛሬ መንጃ ፈቃድ በጉቦ መያዝ ከጉልት በቆሎ የመሸመትን ያህል እንኳን አይከብዱም። ዛሬ ሹፌሮችንና ረዳቶችን ለይቶ ማየት አይቻልም። ሹፌሩ አራራ ይዞት ጫት ለመቃም አንዱ ሥርቻ ጎራ ሲል ረዳቱ መኪናውን ያሽከረክራል። የታክሲው አሽከርካሪ ዕቃ ለመግዛት ሱቅ ሲገባ ወያላው ሁለት ቢያጆ ሰርቶ ይጠብቀዋል። የታክሲው ባለቤት ይህን ሁሉ ጉድ አያውቁም። ቢያውቁም፣ ታክሲው የዕለቱን ገቢ ይዞላቸው እስከመጣ ድረስ ለተሽከርካሪው ደህንነትም ሆነ ለተሳፋሪዎቹ ነፍስ፣ ቅጠል ተሸክማ አስፋልቱን ለምትሻገረዋ ባልቴትም ሆነ ወደ ቄስ ትምህርት ቤት ለሚጓዙት ጨቅሎች አይጨነቁም። እሳቸውስ ቢሆን ምን ያድርጉ – ለሾፌራቸውና ረዳቱ መንጃ ፈቃዱን የሠጠው መሥሪያ ቤትን የሕዝብ ጉዳይ ካልቆረቆረው።
ሥርዓቱ መንጃ ፈቃድ አስጣጡም ላይ ሆነ የበሰለ ልምድ ያላቸው የከባድ መኪና አሽከርካሪዎችን በአግባቡ እንዲሰማሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ነበረበት። ይህ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ላይ የሚታየው የበርካታ ሰዎች ውድ ሕይወጥ መጥፋትም ሆነ የንብረት መውደም ባልተከሰተ ነበር። ሥርዓቱ ዘመናዊ መንገድን ማንጠፍ ብቻ ሳይሆን አነዳድን፣ በርጋታ መቅደምንም ሆነ በመስመሮቹ ማህል ረግቶ የመንዳትን ሥነ-ጥበብ ቀርጾ ትምህርቱን ማሰራጨት ነበረበት። ፈጣን መንገድን ሥልጣኔ ለጎደለው አሽከርካሪ"ፈንጭበትብሎ መልቀቅ ራሱ "ቀይ ሽብርንማፋፋም ነው። ሲኖ ትራኮች "ቀይ ሽብርየተባሉት ለዚህ ነው። ከአዲስ አበባ አዳማ የተዘረጋው አውራ ጎዳና (motor way) ላይ መንዳት ከተክለ ኃይማኖት መርካቶ እየተሽለኮለኩ የመንዳትን ችሎታ ማሳያ መንገድ አይደለም። በፈጣን መንገድ ላይ ፍሬቻ ሳያበሩ መታጠፍ ወደ ሽንኩርት ተራው ተጋፍቶ እንደመግባት ቀላል አይደለም። በዘመናዊው መንገድ መንዳት "ሥልጣኔንእንጂ "አራዳነትንአይጠይቅም። የመንገዶቹን መስመሮች ማህል (driving field)ጠብቆ መንዳት፣ ወደ ሌላ መሥመር ለመግባት ፍሬቻ ማሳየት (turn signal)፣ እስር የተወተፈ መኪና ወይም ሞተር ሳይክል መኖር አለመኖሩን (blind spot) ማረጋገጥ፣ በጥንቃቄ የመቅደም ስልትን (take over) እንዲሁም ፍጥነትን መቆጣጠርና (speed control) ከፊት ካለው ተሽከርካሪ እርቀትን መጠበቅ (safe gap) ወዘተ፣ የመንዳት ችሎታ ብቻ ሳይሆን ሥልጣኔና (civilization) ለነፍሳት ሁሉ የመጠንቀቅ ሠብዓዊነት (humanity) ነው። በከተማ ውስጥ ለእግረኞች ቅድሚያ መስጠት ከሁሉም በላይ አስተዋይነት ነው። ምናልባት መኪና ማሽከርከር ፈቃድ ያላቸውን ዲያስፖራዎችን አሰባስቦ በአውራጎዳና ላይ አነዳድን በኤግዚቢት መንገድ የማሳየት ወርክ ሾፕ ቢዘጋጅ ጠቃሚ ይመስለኛል። ይህን ስል ካገራችን በቂ ችሎታ ያላቸው አስተዋይ አሽከርካሪዎች ጠፍተዋል ማለቴ ሳይሆን የውስጡንም የውጭውንም ልምድ መለዋወጡ ትምህርትን ከመቅሰምያ ዘዴዎች አንደኛው ነው ማሌቴ ነው። አምላክ ሀገራችንን፣ ወገናችንን ይጠብቀን፣ አሜን።

Saturday, March 12, 2016

ኦሮምያና "ልማታዊ ሙስናዎቿ"ከሚክያስ ግዛው (visit my blog  http://michyas.blogspot.no/ )
እኔ እንኳን ወያኔ በፈጠራቸው ዘረኛ የክልል ስሞች አካባቢዎችን መጥራት አልፈልግም ነበር። በዘር፣ ነገድ፣ ጎሳና ጎጥ የሚወሰን የማንነት ግንባታ (identity empowerment) አፍራሽ ይመስለኛል። ብቻ ይሁን እስቲ ወለጋ፣ አርሲ፣ ሐረርጌ፣ ባሌ፣ ወዘተ ማለቱን ትቼ እንደው እንደዘበት "ኦሮምያልበል። ኦሮምያ ውስጥ ሙስና (corruption) እንደ አንድ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ዘርፍ (political economic sector) ተቆጥሮ ዋልጌዎች ሳይፈሩና ሳይሸማቀቁ እየተገበሩት ይገኛሉ። ይህ በደጋግና ጀግኖች ሕብረተሰብ ማህል የተደነቀረው የክፋት ገጽታ የመልካም አስተዳደር መርሆችን (good governance principles)፣ ባህላዊ ትሥሥሮችንና ሥነ-ምግባርን በማጨለሙ ሕዝቡን ለድህነት ዳርጓል። እስቲ እኔ ከታዘብኩት ውስጥ ጥቂቱን ላካፍላችሁ።
እውነት (Truth)፣ እውነት እምነት ነች። ሰዎች ስለአካባቢያቸውም ሆነ የዓለም ዙርያ እንቅስቃሴና ክንውኖች እውነቱን የማወቅ መብት አላቸው። ሰዎች እውነትን ሲረዱ ወደፊት ሊተገብሩ ስላቀዱት ዓላማ ግንዛቤ ይጨብጣሉ። በኦሮምያ የስልጣኑ ባሌቤት ኦሕዴድ ቀድሞውም ቢሆን በእብለት መሠረት ላይ የታነጸ በመሆኑ እውነት ማንጸባረቅ አይችልም። ድርጅቱ ባለቀልም የዋርካ ሥዕል ያለበት ባንዲራ እያውለበለበ ወደ ስብሰባ አዳራሽ ከመንጎድ ውጭ ፋይዳው አይታይም። በአሮምያ ክንውኖች ሁሉ ህፀፅዊ(fallacious) ወደ መሆን ደርሰዋል። በየስብሰባው ውሃ የመይቋጥሩ አረፍተሃሳቦች (fallacious arguments) ይወረወራሉ። ባለስልጣናት ሕዝቡን በመናቅ አደናጋሪና አሳሳች (deceptive, misleading ; fallacious testimony) መረጃዎችን ይበትናሉ። የውስጡ መሠረታዊ ችግር ሳይመረመር ላይ ላዩን የተድበሰበሰ (disappointing; delusive) መፍትሄ መሰል ሃሳብ ቀርቦ ስብሰባው በተዳፈነ ሠላም (fallacious peace) ይጠናቀቃል። በእርግጥ ሁሉንም በአንድ ላይ መጨፍለቅ (generalization) ተገቢ አይደለም። የለበሱትን ሕዝባዊ አደራ በንፃት የሚጠብቁ ቢኖሩም የሙሰኞቹ ጥቁር ሥራ ግን በጎ ክንውኖችን ማጉደፉ አልቀረም። እውነት ኦሮምያ ምድር ሞታ ልትቀበር ትንሽ ቀርቷታል።
መሬት (Land)፣ መሬት በሕዝባዊ መንግሥት ቁጥጥር ሥር ስትውል ልማት ባግባቡ ይፋጠናል። በሃገራችን የመሬት ጉዳይ የፍትህ ጉዳይ አልፋና ኦሜጋ ነው። የተፈጥሮ ኃብት (Natural resources) ከጉልበትና ዓዕምሮ (labour and mental) ጋር ሲዋሃድ ምርትን (production) ያስገኛል። መሬት የተፈጥሮ ኃብት ዋነኛ መፍለቅያ ምንጭ ነች። ማንም ሠላምንና ጸጥታን፣ ልማትንና እድገትን የሚፈልግ ስብስብ የመሬትን ጉዳይ ፍትሃዊ (justify) ለማድረግ ሲል ጠቃሚ መሠረታዊ ህጎችን (system of rules)በቅጡ ይቀርጻል። ይህ ጉዳይ ፈጽሞ ተግባራዊ መሆን ካልቻለ ጥቁር ገበያዎች (black markets) እንደ አሸን ይፈላሉ። ጥቁር ገበያ በሙስና (Corruption) የሚመራ ፖለቲካዊ ምጣኔ ኃብታዊ ፍዳና ዕዳ ነው። መሬት የመንግሥት ኃብት እንዲሆን ፈላስፎችና የምጣኔ ኃብታዊ ሊቆች እጅግ ሠፊ ሳይንሳዊ ትንታኔ ሠጥተዋል። "መሬት ላራሹበኢትዮጵያ ተራማጆች ዙርያ ዘወትር ሲነሳ የቆየ ታሪካዊ መፈክር ነበር። የተጨቋኖችና አጋሮቻቸው እምቅ አስተሳሰብ የወለደው ይህ ታሪካዊ መፈክር ተንቆ ይባስኑ የኦሮምያ መሬት የቀማኞችና ሙሰኞች መገልገያ ሆኗል። በኦሮምያ መሬት አሞሌ ጨው ተሸክሞ ለመጣ ሁሉ በቀላሉ እንደምትቸረቸር ኮማሪት ተንቃለች። መሬት "በሶስተኛ ደላሎችስም እንደዋዛ የምትለወጥ ጉቦኛ ባለሥልጣናትና መዝባሪው ነጋዴ የሚሻሟት አሳዳሪ የራቃት ባለቤት አልባ ሆናለች። መሬት በኦሮምያ ምን ያልሆነችው አለአሜሪካ የተፈጠረችው በቀይ ሕንዶች ደም ላይ ነው። አሜሪካ የተገነባችው በአፍሪካውያን ባርያዎች ግፍና ሰቆቃ ነው። ይህን ግፍ የዲሞክራሲ ቋሚ ምሰሶ ወይም ዓምድ አይደለም። ገዥው መንግሥት ሰዎችን በፌደራል ፖሊስ ጥይት ካስገደለ በኋላ "ለዲሞክራሲው ግንባታ ገና ነን፤ አሜሪካ እስከ ስድሳዎቹ መባቻ ድረስ ሰዎች ይገደሉ ነበርብሎ ያወራል። አገዛዙ ልማቱን እየዘረፈ፣ ሰዎችን እንደ ቀይ ሕንዶች ከቀዪአቸው እያፈናቀለ፣ ጥሬ ሃብቱን ለባዕድ እየቸረቸረና "መሬቴን አትንኩያሉትን ነዋሪዎች እያሽመደመደ "ዲሞክራሲው ገና አልጎለበትምብሎ ያሾፋል። ይህን ትምህርት የቀሰሙት ከሱዛብን ራይስ ከሆነ ያሳዝናል። መልካሞቹን የዲሞክራሲ እሴቶችና የመልካም አስተዳደር መርህን ካደጉት ሃገሮች ተሞክሮ እየቀሰሙ ማዳበር ሲቻል መሬትን ለመቀራመት ብሎ ተወላጁን፣ አገር በቀሉን (indigenous) መግደል የዲሞክራሲ ባህሉም ወጉም አይደለም።
ኢንቨስትሜንት፣ (investment) እኔ ራሴ investment, establishment, department, እንደው ምናለፋችሁ «ment» ያለበት እንግሊዘኛ ሲነገር እፈራ ነበር። ግናስ የሠፈራችን አንድ አጉራ ዘለል "ኢንቬስተርተብሎ ከውጭ ሲመጣ ቃሉን ተለማመድኩኝ። ምን ሊቨሰትር ነውብዬ ስጠብቅ አቀባባይ ረድፈኞችን በእንግሊዘኛ ደልሎ አስደልሎ መሬት ጨመደደ። መሬቱን ደግሞ ሸጦ ገንዘቡን መሬቱን ከሰጡት ከባለስልጣናት ጋር ተካፈላው ሲባል ሰማሁ። በኦሮምያ ብዙ ኢንቬስተሮች ይስተናገዳሉ። ከባለሱቁ አንስቶ እስከትላልቅ ሳሙና፣ ዘይትና ብስኩት ፋብሪካ ድረስ በሙስናው ማህደር ተመዝግቦ በጉቦኛው ማህተም ይለፍ የተመታለት የንግድ ተቋም ሁሉ "እንቬስትሜንትተብሎ ይወደሳል። ባንዳንድ አካባቢዎች የኢንቬስትሜንቱ ባለቤቶች (clandestine wealth) "የማይታዩት ባለስልጣኖችወይንም ተባባሪዎቻቸው ሲሆኑ የንግድ ፈቃዱ የተመዘገበው ባንድ ጭቁን የኢንቬስተሩ ሎሌ ነው። ይህ ዘመናዊ የሎሌነት ሥራ የተቀዳው በቅኝ ግዛት ሥር ከነበሩት የአፍሪካ ሃገሮች ነው።
ስብሰባ (session)፣ አስተማሪያችን "ስብሰባ ሎጂክ (logic) መጠቀምያ ጠቃሚ ጊዜ ነውሲሉ እሰማ ነበር። የፍርድ ሸንጎ ሠብሳቢ የነበረው አጎቴ ደግሞ "የስብሰባ አዳራሽ ዝም ብሎ ተሰባስቦ እንቅልፍና ራስ ምታት መሸመችያ ቦታ አይደለምይል ነበር። ሰው ከተሰበሰበ ንድፈ ሃሳብ አፍልቆ፣ እልባት ያለው ውሳኔ ሸክኖ ለተግባራዊነቱ መንቀሳቀስ አለበት (Theory + practice = Praxis)። ኦሮምያ ስብሰባ ታበዛለች። በሃያ አምስት ዓመታት ኦሮምያ ያስተናገደችው ስብሰባ በሜትር ሲለካ የዓለም ሊግና የተባበሩት የዓለም መንግሥታት ማህበር ካደረጉት ስብሰባ በሶስት እጥፍ ይበልጣል። ምን ንድፈ ሃሳብ ተወረወረምን ተወሰነምን ተፈየደምንም። በእርግጥ እድሜ ለሙስና ሠማይ ጠቅስ ሕንጻዎች ቆመዋል፣ ጥሬ ኃብቱንና ምርቱን ማጓጓዣ ይሆን ዘንድ መንግሥት ዘመናዊ መንገድ አንጥፏል። የሕዝቡ ኑሮ ግን አልተሻሻለም። የሕዝቡ ባህልና እሴቶች ተደፍጥጠዋል። ተሰብሳቢዎች የሙስናንና ጉቦ መርሆችን በሰምና (wax) ወርቅ (gold) አሽሞንሙነው ይለያያሉ። ሰሙ "ሙስና ይጥፋሲሆን ወርቁ ደግሞ"ሙስና እጥፍ ይሁንነው። የመናገር ችሎታ፣ በእጅ የመሄድ አክሮባትና ድፍረት መለማመጃ የሆነው የኦሮምያው ሙስና ወለድ ስብሰባ ብዙ ገንዘቦች አባካኝ ጎጂ ባህል እየሆነ መጥቷል። ሃቀኛ ነጋዴዎች የመንግሥት ገቢ ለመክፈል ማለዳ ወደ አገር ውስጥ ገቢ ሲሄዱ "ፋይሉ አልተገኘምተብለው በኪራይ ሰብሳቢዎች ይባረራሉ። ችግሩን ለማን አቤት ይባላል። አለቆች ስብሰባ ላይ ናቸው። ሃቀኞች ዓመታዊውን ግብርና መንግሥት የደነገገውን ቫት ለመክፈል እንኳን ተቸግረዋል። የመንግሥትን ገቢ ለማስገባት ሙስና ለምን አስፈለገፋይሉ ጠፍቷል በመባሉ ምክንያት ግብር የተቆለለበት ሃቀኛ ነጋዴ ሲጉላላ ማየቱ አሳዛኝ ነው። ይህ ክፋት ኬንያና ናይጄርያም እንኳን አልተከሰተም። በኦሮምያ "ስብሰባሙስናን ማጠናከርያና ኪራይ ሰብሳቢዎችን ማሰልጠኛ ሠንበቴ ከሆነች ሰነበተች።
ፍትህ (justice)፣ በኦሮምያ ፍትህ ደብዝዛለች። ደብዳቢውና ተደብዳቢው ፖሊስ ጣብያ ቢሄዱ ተደብዳቢው ይታሠራል። ዘራፊና ተዘራፊ ሸንጎ ፊት ቢቀርቡ ተዘራፊው ተሸማቆ ከእልፍኙ በአፋጣኝ እንዲወጣ ይደረጋል። ዳኛና ጠበቃ የጥቅም ትሥሥር አድርገዋል። ፍርደ ገምድል ዳኛው የባለጉዳዩን ሳይሆን የጠበቃውን እጆች ያያል። ደህና ጉቦ ሰጪ ጠበቃ ዝናን ያተርፋል፣ በርካታ ደንበኞች ያፈራል። ለፍትህ የቆሙ ጠበቆች ደግሞ ሥራ ፈተዋል። "ፍትህ ይስፈንእያሉ ሲጮኹ ሙሰኛው ዳኛና መሠሪው ጠበቃ ይሳለቁባቸዋል። ፍትህ በኦሮምያ እጅግ ተረግጣለች። ታድያ በአቋራጭ ለመክበር ኢፍትሃዊ ነገሮችን ሳይፈሩ መፈጸም እየተለመደ መጥቷል። በኢፍትሃዊ አሠራሮች ልምድን የቀሰሙት ደላሎችና አቀባባዮች የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ። እነርሱ ለዳኞችና ጠበቆች ሐሰትን አደልቦ እንደምን ማሸነፍ እንደሚቻል ህግን ሳይፈሩ፣ ሰውን ሳያፍሩ ምክር ያካፍሏሉ። ክፉዎች የምክር አገልግሎት በሚሰጡባቸው ቢሯቸው ውስጥ የፍትሃብሄር ህግና መጽሃፍ ቅዱስ ሁለቱም ጠረቤዛው ላይ ተቀምጠዋል። እግርግዳው ላይ ደግሞ "እግዚአብሄር ያያልየሚል በእንግሊዘኛና ኦሮምኛ የተጻፈ ጥቅስ ተሰቅሏል። አይ ዘመን!
አቀባባይ ረድፈኛ ሚና (liaison role between the corruptor and corruptors of public officials) አቀባባይ ረድፈኛ (እንደ ራሴ አተረጓጎምበሙያው ደላላ ያልሆነ ስልታዊ ደላላ ነው። ከደላሎች የሚለየው ነገር ቢኖር ባለስልጣኖችን በጥቅም አሳውሮ መቅረብ መቻሉ ነው (dangerous liaison)። የመናገርና የማሳመን ፣ የማዘበራረቅና የማዛባት ችሎታ የተላበሱት አቀባባይ ረድፈኞች አገዛዙ ባመቻቸው የሙስና መሠላሎች ወደ ላይ የወጡ የዘመኑ አራዶች ናቸው። እነዚህ አቀባባይ ረድፈኞች ጉቦ ሰጪንና ጉበኛን፣ ሠነፍ ተማሪንና ቦዘኔ አስተማሪን፣ ባለስልጣንንና አራጣ አበዳሪውን፣ ፍርደገምድል ዳኛውንና ቆቁን ጠበቃ፣ ወዘተ፣ አገናኝ ናቸው። ካለነዚህ አቀባባይ ረድፈኞች እገዛ ውጭ ባለስልጣን ሊመዘብርና ሙስና ሊቀበል ያዳግተዋል። መሥሪያ ቤቶችን ሁሉ የሙስናና ምዝበራ አርማ ተሸካሚ ያደረጉት እነዚህ በስልታዊ ብረዛ ሳይንስ የተካኑት አቀባባይ ረድፈኞች ዋዛ አይደሉም። ህግና ፍትህ ሚኒስቴር – ሙስናና አድልዎ ሚኒስቴር፣ የንግድ ሚኒስቴር – የምዝበራ ሚኒስቴር፣ የትምህርት ሚኒስቴር – መሃይምነት ማስፋፍያ ሚኒስቴር፣ መከላከያ ሚኒስቴር የጨረታና መሬት ሽሚያ ሚኒስቴር፣ የገንዘብ ሚኒስቴር – የዋጋ ንረት ሚኒስቴር፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር – ኢንቬስትሜንትና ሃዋላ ሚኒስቴር፣ የእርሻ ሚኒስቴር – እንጀራና በርበሬ ላኪ ሚኒስቴር፣ ወዘተ፣ እንዲሆን ሚናውን የተጫወቱት መለኞች ከአስመጭና ላኪዎቹ ወይም ሕንጻ አከራዮቹ ባለስልጣኖች ቢሮ ላፍታም ቢሆን የማይርቁ የሙስናና ዝርፍያው ተቋም (kleptocracy) ባለውለታዎች ናቸው።
ቋንቋ (mother tongue)፣ በኦሮምያ ኦሮሚፋ ብቻ ነው የሥራ ቋንቋ። ልጆቿ ሌላ ክልል ሄደው መሥራት አይችሉም። እሷም ከትግራይ ወይም አማራ አልያም ጋምቤላ፣ አፋር፣ ሶማሌ ወይም ደቡብ ክልሎች የሚመጡትን ልጆች አታስተናግድም። አትድረሱብኝ – አልደርስባችሁም ብላለች። ኦሮምያ አማርኛ ቋንቋን እንደ መጨቀኞ መሣርያ ያህል በመጥላትዋ ሳብያ አፈሯን ፈጭተው፣ ውሃዋን ጠጥተው ያደጉትን ኦሮምኛ የማይችሉትን አንጡራ ልጆቿን እንኳን የጉዲፈቻ ዜግነት ከልክላቸዋለች። ኦሮምያ አማርኛ የነፍጠኞች ቋንቋ መሰላት እንጂ የጋራ መግቢያብያ ቋንቋ ልማትን እንደሚያፋጥን ቴክኖሎጂንም እንደሚያስፋፋ አላጤነችም። አማርኛ የመንግሥት የሥራ ቋንቋ ሆኖ ለብዙ ዓመት ማገልገሉ ማንንም ባልጎዳ ነበር። የሆነስ ሆነና የኢትዮጵያ ሁለተኛ የሥራ ቋንቋ እንግሊዘኛ መሆኑስ ይታወቃልኦሮምያ ይህን የልማት እንቅፋት ሽራ ይልቅስ ብዝህነትን በማስተናገድ የኢትዮጵያ አንድነትን ማጠናከር ቀዳሚ ሚናዋ ሊሆን ይገባል።
ባጠቅላይ ሃቀኝነት፣ ደግነት፣ ፍትሃዊነት፣ ሙስናንና ጉቦን መጸየፍ – እነዚህ የሕዝቡ የመልካም ባህርይ መገለጫ የሆኑት እሴቶች በኦሮምያ ውስጥ ወደ ጉሮኖ ተወርውረዋል። እነዚህን እሴቶች ዳግም ሊያንጸባርቅ የሞከረ ሁሉ መሳለቅያ ይሆናል። ኬንያና ናይጄርያ በሙስናና ጉቦ ጫፍ ላይ የደረሱ ሃገሮች እየተባሉ ሲነገር ቆይቷል። ኦሮምያ ደግሞ በጥቂት ዓመታት ክብረወሰኑን አልፋ የሙስናና ጉቦ ፍልስፍና የተሃድሶ ምድር እንዳትሆን ያሰጋል። ይህን የመሳሰሉት ግፎች ናቸው ዛሬ ሕዝቡን ለአመጽ ያነሳሱት። የፍትህ መዛባት፣ እስር፣ ግድያና የምጣኔ ኃብቱ ይዞታ ልዩነት ካልተገደቡ በቀር ሕዝቡን ለመብቱ ከመታገል የሚያቆመው አንዳች ኃይል የለም። የፌደራል መንግሥቱ እጆች "አመድ አፋሽወይም የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ እንዳሉት"የኢትዮጵያ ሕዝብ ወርቅ ቢያነጥፉለት..."ሆኖ አይደለም ይህ ሁሉ አመጽ የበረከተው። ሙስናው፣ የአስተዳደር በደሉ ኑሮውን አናግተውበት በድህነትና ሰቆቃ ጅራፍ መገረፉ፣ በአምባገነኖች (tyranny, timocracy, oligarchy, plutocracy) ውሳኔ ብቻ መነዳቱ አልበቃ ብሎ ቀማኞች መሬቱንና የመሬቱን የተፈጥሮ ገጸበረከት በጠመንጃ አስገድደው (military command) በጠራራ ፀሃይ ስለሚዘርፉት እንጂ። የእርምቱ እርምጃ ከሰላው ጫፍ ይጀመር።
ጥቂቶቹ የትግራይ ሕወሓት መሪዎች ለም የሆኑትን የጎንደርና ወሎ አጎራባች መሬቶች በማናለብኝነት ተነሳስተው ወደ ትግራይ ክልል መደባለቃቸው ያስከተለውን አደጋና የህዝብ ቁጣ በሚቀጥለው ጊዜ እዘግባለሁ።
እግዚአብሄር ቸር ዘመን ያምጣልን፣ አሜን

Tuesday, March 8, 2016

የነብርን ጭራ አይዙ ከያዙ አይለቁ!
እነሆ እኛ ኢትዮጵያዉያን ህብረት፣ መደጋገፍ፣ ስምምነትና አርቆ አሳቢነት የሚጠይቅበት ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል። ያለፉት ዓመታት የወያኔውን ጥቁር ሥርዓት ምንነት አሳይቶናል። ይህንን ብቻ አይደለም፤ በአምባገነን ሥርዓትና ለቅኝ ገዥዎች በባንዳነት በሚያድር ሥርዓት መካከል ያለውን ልዩነትም በሚገባ አሳውቆናል። የንጉሡ ዘመን ኋላ ቀር ነበር። የደርግ ዘመን አምባገነን ነበር። በሁለቱም ሥርዓት ወቅት ግን ሃገር ነበረች። ኢትዮጵያ እስከ ባህረ በሯ ሉዓላዊ እስከ ሕዝቦቿ ክቡር ነበረች። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ወያኔ ዘረኛ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሙስናዊ አምባገነን ሥራዓት ቋሚ ተጠሪ ስብስብ ተቋም ብቻ አይደለም። ወያኔ "የአናቁረህ ግዛ" ግፍ አራማጅ ብቸኛ የቀማኞች ድርጅት ብቻ አይደለም። ወያኔ ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያን ለውጭ ባለሃብቶች የሸበሸበ የኃጢአተኞችና "የአስረሽ ምቺ" ዳንኪረኞች፣ መዝባሪዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሁሉም የኃጢዓት ሥርዓቶች ድምር ነው። ወያኔ ድንገት ከተሰባሰበበት ደደቢት ሸለቆ ተንከባሉ ሠይጣን ዋሻ ውስጥ ለአመታት ከርሞ ዲያቢሎስ ሳያኝክ የተፋው የርኩስ ሥርዓት ቁንጮ ነው። እድሏ ሆኖ ቅድስት ኢትዮጵያ የዚህ ሥርዓት ተሸካሚ ሆናለች። እንዲያ እንዳልተከበረች፣ እንዲያ እንዳልተፈራች ሃገራችን ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ቅርጫ ቀረበች። ሥርዓቱ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ኢትዮጵያን በቁሟ የገነዘ፣ ሕዝቧን ያስጨነቀ መሪር ሥርዓት ነው። ኢትዮጵያ ሃገራችንን ከዚህ ሥርዓት የሚገላግላት ቆራጥነትና በህብረት መነሳት ብቻ ነው። ህዝብን በመርዘኛ ራዕይ ሰልቦ፣ ወጣቱን በሥራ አጥነት አጠውልጎ ለስደትና ሴተኛ አዳሪነት እየዳረገ፣ ነዋሪውን በልማት ስምና በከተማ ማስፋፋት እያፈናቀለ ሕዝብን በቅኝ ገዥዎች ቋንቋና በምጣኔ ኃብት እድገት እያደናገረ የሃገሪቱን ሃብት መዝብሮ ወደ ውጭ በማሸሽና በከፍተኛ ዕዳ ውስጥ በመዝፈቅ በጥቂቶች ስም ሃብት እያከማቸ እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊገዛ የሚቃጣ ዘመነኛ የግፍ ሥርዓት አራማጅ ወያኔ ብቻ ነው።
በዘረፉት ገንዘብ ልጆቻቸውን እንደ ልዑላውያን ልጆች በምዕራቡ ዓለም ወይም ቻይና በቅምጥል ሊያኖሩ የሚያስቡ ሞኞች ወቅቱን ያልተገነዘቡ ብቻ ናቸው። ከጭቁን ሕዝብ በተመዘበረ ነዋይ ኬክ ገዝቶ መዘመር፣ ሻምፓኝ አንስቶ ጤንነትን መመኘት ሲዖል አፋፍ ቆሞ ዲያቢሎስን መጋበዝ መሆኑን እንዲሆም ከረሃብተኞች በተነጠቀ ገንዘብ በተገዛ ሸማ መዋብ በደም በተለወሰ ክር የተሰፋ መሆኑ ገና ያልገባቸው ይልቁንም የሥርዓቱ መበስበስ ገና ያልታያቸው ርህራሄ ቢሶች ብቻ ናቸው። ከድሆች መሬት ነጥቆ በሙስና፣ በዘረፋ በተገነቡ ዘመናዊ ሕንፃ ውስጥ መኖር ጥልቅ ጉድጓድ ውስጥ መቀበር መሆኑ ገና ያልገባቸው እብሪተኞች ብቻ ናቸው። ከድሆች አፍ በተነጠቀ ገንዘብ ሠማይ ጠቀስ ፎቆቻቸውን ወደ ላይ አንጋጠው የሚመለከቱ የፀሃይ ብርሃን የማትጠልቅ የሚመስላቸው መሃይማን ብቻ ናቸው። ግንዛቤ ያጠራቸው ባለስልጣናትና ልጆቻቸው የሙስናው ተጠቃሚዎች፣ ገና በሼራተንና ሂልተን አልኮል የሚራጩት፣ የሉካንዳው ቤት ሠልፈኞች፣ የዳንኪራ ቤቱ ጋጠ ወጦችም ጭምር ሕዝባዊው ሱናሜ መምጣቱን ፈፅሞ ያልተገነዘቡት ዘመኖች ናቸው። እነርሱ በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደሚፈነጥዙ ዓይነት የግፍ ሥሪቶች ናቸውና የገናናዋ ኢትዮጵያ እንባ ያቅበዘብዛቸዋል። የገባቸው፣ አዎ የገባቸው ገዥዎች፣ ነገ ዓይደለም ዛሬውኑ ራሳቸውን ነፃ ያወጣሉ። የገባቸው፣ የአምላክ ምህረት የቀረባቸው፣ ይቅርታ ጠይቀው መጪው ዘመን ለነሱም ለሃገሪቱም ብሩህ እንዲሆን ይተጋሉ። የገባቸው፣ ልባቸው ያልደነደነው የግፍ ሥርዓት ፈጽሞ እንዲቀበር የሚመኙ የሕዝቡን ጥያቄ ይቀበላሉ። የገባቸው፣ የድሆች እንባ ሲንቆረቆር አይተው ልባቸው በርኅራሄ የረሰረሰው አዲስ ታሪክ ይሠራሉ። ያዘኑ፣ የረሃብተኛውን ሕጻን አጥንት የቆጠሩ የነጠፉ ጡቶችን አይተው የሚያለቅሱ ገዥዎች ሥልጣናቸውን በሠላም ለህዝብ ያስረክባሉ። ዕድሉ አሁንም አለ። ይህ ዕድል ነገ ላይኖር ይችላል። ሳዳም ሁሴንና ጋዳፊ፣ ያውም ሃገራቸውን ከልብ የሚወዱት እንኳን ይህ ዕድል አምልጧቸዋል። እናንተስ?
ዛሬ የበደሉ ጽዋ ሞልቶ ቢፈስ ሕዝብ በቁጣ ተነስቷል። ሕዝብ በቃኝ፣ መረረኝ ብሏል። ሁሉም ሊተባበርና ከትግሉ ጎን መሰለፍ አለበት። ዛሬ አማራ፣ ኦሮሞ፣ ጉራጌ፣ አፋር፣ ትግራይ፣ ወላይታ፣ ሲዳማ፣ አኙዋክ፣ ከንባታ፣ ከፊቾ እያልን የገበጣ ጨዋታ የምንጫወትበት ወቅት አይደለም። እኛ ኢትዮጵያውያን እንደቀድሞ ተታለን አንድ የበሰበሰሰ ሥርዓት በሌላ አፋኝ ሥርዓት ሲተካ አይተን ዝም የምንል ወይንም ወያኔ አንዱን ዘር ካንዱ ሊያጋጭ በተለመው "የአልሞት ባይ ተጋዳይ" ስልቱ ውስጥ የምንዘፈቅለት ቂሎች አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያውያን ትግሉን አመካኝቶ ሌላ ነውጥ ሊያመጣ የሚችል ኃይልን እሹሩሩ የምንልም አይደለንም። እኛ ኢትዮጵያውያን ከዚህ በኋላ ፈጽሞ አንከፋፈልም። የወያኔው ሥርዓት የጥቁር አምባገነንነትን ቀለም፣ የአንድ ዘር የበላይነት የቅኝ ገዥዎች ቅጅ የግፍ አገዛዝ መርህን፣ የእብለት አካሄድንና የሸፍጥ ስልት ፖለቲካ ምንነትን እንድናውቅ አስችሎናል። በእርግጥ ዘረኝነትንና ልዩነትን አሽቀንጥረን በኅብረት እንድንታገል፣ በአንድ ላይ እንድንቆምም ትምህርት ሆኖናል። በልማት ስም ቅኝ አገዛዝዝን በዲሞክራሲ ስም ጭለማ ያመጣብንን ሥርዓት ሁላችንም መርምረነዋል። እነሆ ዛሬ - ሁላችንም በአንድነት "መሬት ላራሹና" "ሕዝባዊ መንግሥት" ይመስረት መፈክሮችን የምንተገብርበት ወሳኝ ዘመን ላይ ደረስናል። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከዳር እስከ ዳር በአንድነት ተነስቷል። ዛሬ የተጀመረው ሕዝባዊ ትግል ቢዳከም እንደገና መቀመቅ ውስጥ የምንገባው እኛው ነንና ትግሉን ይበልጥ ማፋፋም አለብን። "የነብርን ጭራ አይዙ - ከያዙ አይለቁ!
ሕዝብ ያሸንፋል፤ ኢትዮጵያ እንደቀድሞዋ በነጻነትዋ ትራመዳለች። ኢትዮጵያ ግርማ ሞገሥዋ ይመለሳል።
ሚክያስ ግዛው