ወያኔ ማንነቱን ሕዝቡ ጠንቅቆ ከማወቁና በሚፈጽማቸው በደሎችና ግፎች ከመንገሽገሹ የተነሣ በተፈጠረበት እጅግ በጣም ከባድ በራስ ያለመተማመን ችግር እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ለተቃዋሚ ወይም ለተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከገዛ ሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎች በተጻራሪ ነጻነታቸውንና መብቶቻቸውን እየከለከለ በራሱ ፍላጎት ብቻ በጠባቡ ከልሎ የሚሰጣቸውን የመጫዎቻ ሜዳም እንኳን ሊሰጥ በፍጹም አልፈለገም፡፡ እንደወያኔ አስተሳሰብ ይሄ ስልቱ ጊዜው አልፎበታል ፡፡ ቢያደርገው “ልቆጣጠረው በማልችለውና ባልጠበኩት አቅጣጫ ሄዶ ያስበላኛል” ብሎ ያምናል፡፡ በመሆኑም ብቻውን ሮጦ አሸነፍኩ ብሎ በማስጨብጨብ አሁንም መንግሥት ነኝ ሊል ፈልጓል፡፡
No comments:
Post a Comment