Thursday, November 27, 2014

"ሕዝባው መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቅል" ወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ"

"ሕዝባው መንግስት"፣ "ሕዝባዊ መፈናቅል" ወይንስ "ሕዝባዊ መፍረስ"
ሚክያስ ሙሉጌታ ከ ኖርዌ
ድሮ ከዘውዱ መገርሰስ በፊት አዲስ አበባ እንደህ እንዳሁኑ ጭንቅንቅ ያላለች ለመሆኗ ትላልቆች ሲናገሩ እሰማለሁኝ። ብዙ
ሰዎች እርስ በእርሳችን እንተዋወቅ ነበር፣ ያለው ለሌለው ያዝናል፣ አውደ አመቱን በጋራ እናከብራለን ይላሉ። ቤት ገብቶ
የሚዘርፍ ሌባ ቀርቶ የተሰጣን ልብስ እንኳን ከውጭ አንስቶ የሚሰወር ወስላታ እምብዛም አይታይም ይላሉ። ሁሉም
በአቅሙ ሰርቶ ስለሚኖር የሰው እጅን መመልከት ነውር እንደነበርም ያወሳሉ። ሕዝቡ እግዚአብሄርን በጽኑ ያመልካል፣
በኢትዮጵያዊነቱ ይመካል፣ ባንዲራውን ይወዳል፣ ንጉሱንም ያከብራል፣ እያሉ ትላልቆቹ ዘወትር ሲያወሩ በጽሞና
አዳምጣለሁኝ።
እኔ የማውቃት አዲስ አበባ ግን ታላላቆቼ እንደሚያወሩላት አይደለችም። ምንድነው ምክንያቱ አልኳቸው? "ቀድሞ
ክርስትያኑና እስላሙ ተፋቅሮ የሚኖርባት፣ ባህልና ወጉ የሚናፍቁባት፣ ግብረገብነቱና ጨዋነቱ ጥልቅ የነበሩባት፣ የምሁሩ
እውቀትና የሕዝቡ ማስተውል እንደ እንቁ የሚብለጨለጩባት፣ ኪነቱ፣ ቴያትሩና ስነ ጥበቡ እውነትንና እምነትን
ሲያንጸባርቁባት የነበረችው አዲስ አበባ ዛሬ በክፋት ሠራዊትና በሙስና ባለሃብቶች በመወረሯ ነዋ" አሉኝ። በእርግጥ እኔም
እንደታዘብኩት የአዲስ አበባ መሬት ካቅሟ በላይ በስርቆት በተገነቡ ሕንፃዎች፣ በዳንኪራ ቤቶች፣ መሸታ ቤቶች፣ ቅባት
ቤቶች፣ የውበት ሳሎኖች፣ ላውንደሪዎች፣ መኪና አከራዮች፣ ወዘተ ተጨናንቃለች።
የኢጣልያ የቅኝ ገዢነት ሕልም ለማብከን መኳንንቱ የመከሩበት የእምዬ ሚኒልክና የነብር አራስዎ እቴጌ ጣይቱ መናኸርያ
ያ ታላቁ ቤተ መንግስት ኢትዮጵያን በማይወዱት ሰዎች ተይዟል። የንጉሠ ነገስቱ ኃይለሥላሴ ማደርያ ኢዮቤልዩ ቤተ
መንግስትም ተደፍሯል። ደርግ ታላላቆቹ የሀገር ኃብት የነበሩትን ወደር የለሽ ምርጥ ምሁራን ቢገድልም አብዛኛዎቹን ንጉሱ
ያስተማሯቸውን ብቁ ምሁራን ተጠቅሞባቸው ነበር። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ብቃቱ ፈጽሞ የሌላቸው የወያኔ የጫካ ሽፍቶች
የመንግስት መዋቅሩን ሲያዛንፉ አዲስ አበባ ዝም ብላለች። ማስተዋልና ጥበብ የሌላቸው ሁሉ ስልጣነ-መንግስቱን
ሲቀልዱበት አዲስ አበባ እንዴት እንዳስቻላት አላውቅም። ሌላም ጉድ አለ። የእግዚአብሄር ሰዎች የነበሩት ፓትርያርኮቹ
አቡነ ቴዎፍሎስ፣ አቡነ ተክለሃይማኖትና አቡነ መርቆርዮስ በታጋዩ አባ ጳውሎስ ሲተኩ ሕዝበ ክርስትያኑ በፍርሃት ተውጦ
ስልጣነ-ክህነቱንና ቅዱስ ሲኖዶሱን አስደፍሯል።
አዲስ አበባ ከየአራቱ ማዕዘናት የተሰባሰቡት የእትዮጵያ ሕዝቦች ባንድነት የሚኖሩባት ማዕከል በመሆንዋ የሀገሪቱን
ፖለቲካዊ ጥያቄዎችንም ለመንግስት የምታቀርበውም እሱዋው ነች። ቀደም ሲል በመላ ሃገሪቱ የሚገኙት ተማሪዎች
የንጉሱን አስተዳደር በመቃወም እጅግ እልህ የተሞላበት ትግልን ማድረጋቸው ሲታወስ፣ ለመንግስቱ ቅርበት ያላቸው
የአዲስ አበባው ተማሪዎችም ደግሞ ስርዓቱ ማስተዳደር እስቂያቅተው ድረስ ተናንቀውታል። በወሬ የምሰማው ''መሬት
ላራሹና" - "ሕዝባዊ መንግስት" ይመስረት መፈክሮች - መፈክሮች ብቻ ሳይሆኑ የታጋዩ ልበ ሙሉነትንን ማንጸባረቅያ
የሕዝቦች ሙሉ መብት እንደነበሩ ነው። ታጋዩ በየተራ ሲሞት ጥያቄዎቹ ግን እስካሁን መልስ አላገኙም። ያለፈው ወጣት
መሬት ላራሹ በማለቱ በንጉሱ ወታደሮች ተደብድቧል ተብሏል። ቀጥሎም ሕዝባዊ መንግስት በማለቱ በደርግ ቀይ ሽብር
ተገድሏል አሉ። የዘንድሮው በኔ ዘመን የተከሰተው ለየት ያለ ነው። ወጣቱ "ስብዓዊ መብት ይከበር" - "ሕዝባዊ
መንግስትም" እንዳይል ታፍኖ ስለ ስደት ብቻ እንዲያውጠነጥን ተደርጓል። እነአንዷለም፣ እስክንድርና ርዕዮት የመሳሰሉት
ብቸኛ ቆራጦች የቀድሞውን ወጣት ታሪካዊ አደራ ተሸክመው ሕዝባዊ መንግስት በማለታቸው ቃሊቲ ተወርውረዋል።
ከላይ በጽሁፌ ላይ እንደጀመርኩት አዲስ አበባ ዛሬ የተጨናነቀችው በተፈናቃዮችና በወሮበሎች ብዛት እንጂ የልማቱ
እንቅሳቃሴ በወለዳቸው ሠራተኞች አይደለም። አዲስ አበባን ጨምሮ ሌሎች ከተሞች ሳይቀሩ በጎዳና ተዳዳሪዎች፣ በሴተኛ
አዳሪዎች፣ በልመናና በሸክም በሚተዳደሩ፣ ጥቃቅን ሥራዎችን በሚፈልጉ ችግረኞች፣ ትምህርታቸውን በጨረሱ ሥራ
አጦች፣ በቀማኞችና ማጅራት መችዎች፣ በወያኔው ደህንነቶችና ፖሊሶች፣ ከተለያዩ ሀገሮች በመጡ ሴት አሳዳጆች፣ ጎጂ
ዕጾችንና ጫትን በሽያጭ በሚያስፋፉ ወሮበሎች፣ የሀገሪቱን ጥንታዊና ታሪካዊ ቅርሶችን ከሀገር በሚያስወጡ ዘራፊዎች፣
ሴት እህቶቻችንን ለአረቡ ሀገራት በሚያከፋፍሉ ደላሎች፣ በኮንትሮባንድ ሥራ በተሰማሩ አታላዮች፣ ወጣቱን ለስደት
በሚያሰማሩ አስኮብላዮች፣ ወዘተ ተሞልተዋል። በንጉሱ ዘመንም ሆነ በደርግ ዘመን ሕዝቡም እንዳቅሙ በልቶ ያድር ነበር
ይባላል። ዛሬ ግን ተጠቃሚዎቹ የሀገሪቱን ኃብትና ቅርስ መዝባሪዎቹ፣ ሙስናውን ከመጠን በላይ ያደለቡት ባለስልጣኖቹና
እነሱን ተገን ያደረጉት ወገነተኛ ነጋዴዎችና ዘራፊዎች ሲሆኑ ሕዝቡ ግን በረሃብ እየተቀጣ የብቀላ ርምጃ እየተወሰደበት
ነው።
ወያኔ ብዙዎችን ከቀያቸው ወይም ከሰፈራ ጣብያቸው እያፈናቀለ በየከተሞች እንዲሰበሰቡ ያደርጋል። የጋምቤላ ሕዝብ
መሬት ለሕንዶቹ ተሰጥቷል። የኦሞ ሸለቆው ድንቅ ሕዝብ መሬት እየተቀማ ለባዕዳኑ ሊሰጥ ነው። የአፋሮቹም መሬት
በሸንኮራ እርሻ ሳብያ እየተቀማ ነው። ወያኔ ዋልድባ የመሳሰሉትን ገዳማትን በማፍረስ ክርስትያኑን ሳይቀር በማፈናቀል ላይ
ይገኛል። በበደኖና በአርባጉጉ እንዳላስጨፈጨፉት ሁሉ ከደቡብ ኢትዮጵያ ቤንች ማጂ ዞን ጉራ ፋርዳ ወረዳ ለቀህ ውጣ
በማለት ይህንኑ መከረኛ አማራ እፈናቀሉት። ይህ ሁሉ ችግረኛ ሕዝብ ከተሞችን እንዲያጨናንቅ ሆን ተብሎ የሚሰራ ራሱን
የቻለ የወያኔው ሕዝብን የማፈናቀል ሥራ ከግፍ አገዛዙ መርሃ ግብር አንዱ ነው። ዓላማው ሕዝቡ በመንግስቱ ላይ
ከመነሳቱ በፊት በወሮበሎቹና ዘራፊዎቹ እርስ በእርሱ እንዲጨራረስ የተወጠነ ሰይጣናዊ ተልዕኮ ነው። ወያኔ በቅንጅቱ
ከተሸነፈ በኋላ ውስጥ ውስጡን ሲሰራው የነበረው ይህ ሕዝቡን የማፈናቀሉ ሥራ ድህነትን በየገጠሩ ማስፋፋትና ማህበራዊ
ቅራኔዎችን በከተሞች በማባባስ የአገዛዝ ዘመኑን ማስረዘም ነው። ባጠቃላይም ወያኔ ከተሞችን እንደ ኮንሴንትሬሽን ካምፕ
በመጠቀም ገጠሪቱን ኢትዮጵያ ላባዕዳኑ ኃይል በመሸጥ ላይ ነው።
አቶ መለስ የሀገሪቱን ችገር እኮ አስቀድመው ራሳቸው ነግረውን ነበር። "እድላችን ሆኖ ጠንካራ ተቃዋሚ አላገኘንም" -
ነበር ያሉት። አባባላቸውን ጠልቆ ሲረዱት እርሳቸው ወንበሩን በመቆናጠጣቸው ተቃዎሚዎችን ማንም እንደማይረዳ
የሚጠቁም ነበር። ቀጥለውም " አዲስ አበባ ፎቅ በፎቅ ሆናለች እየተባል ከዳር ዳር ይወራል - በእርግጥ ማንም ከደረጃ
በታች የሆነ ፎቅ በዘመናዊ ፎቅ ሲተካ የማይወድ የለም - ነገር ግን ከዚህ ሁሉ ፎቅ ማህል አንድ ሶስተናው እንዱስትሪ
ቢሆን ኖሮ በልማቱ ላይ ከፍተና እድገት ያሳይ ነበር" - ብለዋል። ንግግራቸው ሕዝቡ ላይ ለማሾፍ ብቻም አይደለም። ፎቁ
በሙስና ሲገነባ ዝም ብለው ችግሩ ሲባባስ ማማሃኛ ፈለጉ። ችግሩን ወያኔ ሆን ብሎ የፈጠረው እንዳይመስል የማደናገርያ
የፖለቲካ ስልት ተጠቀሙ። ከምርጥ ንግግሮቻቸው ማህል ግን ይህን አባባላቸው ሁላችንንም የሚያነቃ መሆን ይገባዋል።
"መሬቱን ሊያለማ የሚመጣው አረቡ፣ ቱርኩና ሕንዱ ነው። ወደድንም ጠላንም ነገ ሀገር የሌለን ባይተዋር ነው
የምንሆነው" – ብለዋል። ወያኔዎቹ አስተዳደሩ ሲያቅታቸው ሀገሪቱን ለባዕድ ሸጠው ወይንም ኢትዮጵያን ለማፍረስ
ላደፈጡ ጠላቶችዋ አሳልፈው ሰጥተው ሕዝቡን ለመከራ አጋልጠው እነሱም ዶግ አመድ ሆነው እንደሚቀሩ አቶ መለስ
ተንብየው እስከወድያኛው አሸለቡ።
እድላችን እንዳይሰምር ሆኖ የሕዝባዊ መንግስት ጥያቄአችን እስካሁን መልስ ሳያገኝ ወደ ሕዝባዊ መፈናቅሉ አሸጋግሮናል።
ሕዝባዊ መፈናቅሉ ወደ ሕዝባዊ መፍረስ ሊያሸጋግረን ጥቂት ይቀራል። የዘመናቱ ባሕላዊው የዘውድ ሥርወ መንግስትና
የሀገር ሠራዊት ተንዷል፣ የሀገር ጥቅምና ሕልውና አስከባሪዋ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያን በኢአማኞችና
ዓለማዊ ሴረኞች ተመዝብራለች። በደሙና በስጋው ዋጅቶ የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ያስጠበቀው
ኢትዮጵያዊውን ልጅና የልጅ ልጆች ማፈናቀሉና ማሰደዱ ሀገሪቱን የማፍረሱ ቀጣይ ምዕራፍ ሆኗል። ዛሬ ከመንግስት
ሥልጣን ጠያቂነት ወደ ታች ወርደን ሀገርን ወደ ማዳን ደረጃ ተሸጋግረናል። ኢትዮጵያ ስትዳከም ፈንጠዝያው
የምዕራብያኖቹ ወዲህም የአረቦቹ ነው። ወያኔ የምዕራቦቹና አረቦቹ ባለሙሉ ስልጣን እንደራሴ እንጂ እንደ ኢትዮጵያ
ሕዝብ ተወካይ ሲሰራ አልቻለም።
ከዚህ በኋላ ምን አይነት የትግል ስልት መከተል እንደሚኖርብን ግራ ተጋብተናል። የሃገሪቱ መፍረስ ግን የደቡቡን ሕዝብ፣
ኦሮሞውን፣ ትግሬውን፣ አማራውን፣ ጋምቤላውን፣ አፋሩን፣ ኦጋዴኑን፣ ባጠቃላይም መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ የሚመለከት
ትልቅ አደጋ እንደሆን ልንረዳው ይገባናል። ጥያቄአችን የዲሞክራሲና የሕዝባዊ መንግስት መሆኖ ቀርቶ ሀገር የማዳኑ
ሆኗል።
እነዚህኑ መከራዎችና ግፎችን አስመልክቶ ብዙ ተጽፏል። ብዙ ውይይቶች ተደርገውበታል። በሀገር ቤት በሚኖሩም ሆነ
በውጭው በሚኖሩ ምሁራንም ብዙ ትችቶችና የተቃውሞ ጽሁፎች ቀርበዋል። ይህ ሁሉ የሰላም ትግል ወያኔ ሥርዓቱን
እንዲያሻሽል ወይም ሕዝብ በመረጠው መንግስት እንዲተካ ነበር። ግን ፈቀቅ ያለ ነገር የለም። የዋጋው ግሽበትና የድህነቱ
መስፋፋት ሕዝቡን አዳሽቆታል። ሕዝባችን ተሰዶ ሊያልቅ ነው።
ኢትዮጵያውያን ሁላችን ሃገር ከመፍረሷ በፊት አንድ ሃሳብ አንድ ልብ ሆነን አገርን ለማዳን በቆራጥነት እንዳይነሳ
ያላስቻለልን መንፈሳዊ ብክለት በቅጡ ልንመረምር ይገባል።
ሕዝባዊ መንግስት ስንል ስንጮህ የነበርን እንደዋዛ ሕዝብ የማፈናቀሉን የጉራፈርዳንና የቤንሻንጉሉ ፖለቲካን በአይናችን
ተመለከትን። ነገን ብንጠብቅ የባሰ ነው። ዛሬውኑ በአንድነት ተነስተን ሕዝባዊ መፍረሱን መታደግ አለብን።
በቸር እንሰንብት
ሚክያስ ሙሉጌታን በዚህ አድራሻ ማግኘት ይቻላል michyas.ethio@yahoo.com

ESAT Daily News Amsterdam November 26 2014 Ethiopia | ESATTUBE

ESAT Daily News Amsterdam November 26 2014 Ethiopia | ESATTUBE

Wednesday, November 26, 2014

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

ታሪክን ማደብዝዝም ማጥፋትም አይቻልም!

Nov 23, 2014
በአለማችን በተለይ አፍሪካ ዉስጥ የአገርን ብሄራዊ ኃብት የሚዘርፉ፤የህዝብን መብት የሚረግጡና አገርን እነሱ ባሰኛቸዉ አቅጣጫ ብቻ ይዘዉ የሚነጉዱ አያሌ ፈላጭ ቆራጭ መንግስታት አሉ። እነዚህ ህዝብን የሚበድሉ መንግስታት ሁሉም በጥቅሉ አምባገነን ይባሉ እንጂ በመካከላቸዉ ጎላ ብሎ የሚታይ ትልቅ ልዩነት አለ። ሀኖም የቱንም ያክል ልዩነት ቢኖርም እንደ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች እንመራዋለን የሚሉትን ህዝብ የሚንቁና የኛ ነዉ የሚሉትን አገር የሚጠሉ አምባገነን መንግስታት የሉም፤ በታሪክም ኖረዉ አያዉቁም። አምባገነን መንግስታት የስልጣን ዘመናቸዉን ለማራዘምና ከስልጣን ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ክብር፤ ዝናና ጥቅማ ጥቅም እንዳይቋረጥ ሲሉ የሚቃወማቸዉንና ለስልጣን ዘመናቸዉ አደጋ ነዉ የሚሉትን ሁሉ ያስራሉ፤ ይደበድባሉ ወይም ይገድላሉ። እነዚህን ነገሮች የወያኔ መሪዎችም ያደርጋሉ፤ ነገር ግን በወያኔና በሌሎቹ አምባገነን አገዛዞች መካክል እጅግ በጣም ትልቅ ልዩነት አለ። ለምሳሌ ወያኔዎች ዘረኛ አምባገነኖች ናቸዉ፤ የወያኔ መሪዎች ኢትዮጵያን እንደ ጥገት ላም አንጂ እንደ አገራቸዉ አይመለከቱም። ከዚህ በተጨማሪ ኢትዮጵያን፤ ህዝቧንና ታሪኳን ይንቃሉ፤ ያንኳስሳሉ።
ባለፉት አምስትና ስድስት አመታት በግልጽ እንደተመለከትነዉ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ገበሬ ከመሬቱ አፋናቅለዉ ለምለም መሬቱን ለባዕዳንና ለህወሓት የጦር መኮንኖች ሰጥተዋል። መሬቴንና ቤቴን አልለቅም ብሎ የተቀናቀናቸዉን ደግሞ በጅምላ ገድለዋል። በከተሞች ዉስጥም ከተሜዉን ምንም ካሳ ሳይከፍሉት ዕድሜ ልኩን ከኖረበት ቤቱ እያፈናቀሉ ከነቤተሰቡ ሜዳ ላይ ጥለዉት መሬቱን ባለኃብት ለሚሏቸዉ የወያኔ ባለሟሎች ሰጥተዋል። በአጠቃላይ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ አንድነት፤ በታሪኳና በህዝቧ ላይ እንዲህ ነዉ ተብሎ ለመናገር የሚዳግት ትልቅ በደል ፈጽመዋል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በእናት አገራችን ላይ ያደረሱት በደል ተዘርዝሮ የሚያልቅ አይደለምና ዛሬ ወደዚያ ዝርዝር ዉስጥ አንገባም፤ ዛሬ ትኩረት የምንሰጠዉ ወያኔ ደግሞ ደጋግሞ ከዘመተባቸዉና ሙሉ ኃይሉን ካሳረፈባቸዉ የአገራችን እሴቶች አንዱ ታሪካችን ነዉና የዛሬዉ ቆይታችን በዚሁ በታሪካችን አካባቢ ይሆናል።
ታሪክ በአንድ አገር ዉስጥ እያንዳንዱ ትዉልድ ከሱ የቀደመዉ ትዉልድ በግል፤ በቡድንና በማህበረሰብ ደረጃ የተጓዘበትን መንገድ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ካለፈዉ የምንማርበትና የወደፊቱን ጉዟችንን ለመጀመር በመረጃነት የሚያገለግለንን እዉቀት የምናገኝበት የጥበብ ድርሳን ነዉ። የማንም አገር ታሪክ ዉብ ሆኖ የሚያምርና የማያምር ሁለት ገጽታዎች አሉት፤ የማያምረንን የታሪክ ጠባሳ ወደ ኋላ ሄደን ማከም በፍጹም እንደማንችል ሁሉ የወደፊቱን ታሪካችንንም የብዙ ማህበረሰባዊ መስተጋብሮች ዉጤት ነዉና ያሰኘንን ቅርጽና ይዘት ልንሰጠዉ አንችልም። የታሪክ ዋናዉና ትልቁ ቁም ነገር የታሪኩ ባለቤት የሆነዉ ማህብረሰብ እራሱን ወደ ኋላም ወደ ፊትም የሚመለትበት መስኮት መሆኑ ነዉ። ምንም አይነት ታሪክ የሌለዉ ህብረተሰብ የለም፤ ካለም ከየት አንደመጣና ወዴት አንደሚሄድም አያዉቅም።
አገራችን ኢትዮጵያ ረጂምና ጥንታዊ ታሪክ ካላቸዉ ጥቂት አገሮች ዉስጥ አንዷ ናት። ይህ ረጂም ታሪካችን ደግሞ አንገት ቀና የሚያስደርግ የድልና የገድል ታሪክ አንደሆነ ሁሉ አንገት የሚያስደፋ የግፍና የበደል ታሪክም አለበት። የዛሬዉ ትዉልድ ኢትዮጵያዊ ካለፈዉ ታሪኩ ከበደሉም ከገድሉም ተምሮ የወደፊት አካሄዱን ከሞላጎደል መቆጣጠር የሚችል እድለኛ ትዉልድ ነዉና አባቶቹ ባቆዩለት ታሪክ ሊኮራ ይገባል። አንድ ህዝብ በታሪኩ እንዲኮራ ደግሞ ታሪኩ በተደጋጋሚ ሊነገረዉ ሊተረክለትና በጽሁም መልክትም በገፍ ሊቀርብለት ይገባል። የአገራችን የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ለዚህ የታደለ አይደለም ፤ ምክንያቱም እንመራሀለን የሚሉት መሪዎቹ ታሪኩን የሚያንቋሽሹና የሚንቁ መሪዎች ናቸዉ።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ካደረሱትና ዛሬም በማድረስ ላይ ካሉት በደሎች አንዱና ዋነኛዉ የኢትዮጳያን ታሪክ ለባዕዳንና የታሪኩ ባለቤት ለሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ አሳንሰዉና እንደ ተራ ዕቃ አቃልለዉ ማቅረባቸዉ ነዉ። የወያኔ መሪዎች አዲስ አበባን ሲቆጣጠሩ መጀመሪያ ከተናገሯቸዉ ንግግሮች አንዱ የኢትዮጵያን ህዝብ ታሪክ የመቶ አመት ታሪክ ነዉ ያሉት አስቀያሚ ንግግር ነዉ። በዚህ አባባል ላይ የጸና አቋም ካላቸዉ የወያኔ መሪዎች ዉስጥ ዛሬ በህይወት የማይገኘዉ መለስ ዜናዊና ጓደኛዉ ስብሐት ነጋ ዋና ዋናዎቹ ናቸዉ። የሚገርመዉ እነዚህ የኢትዮጵያን ታሪክ በአንድ መቶ አመት የወሰኑት ሁለት ግለሰቦች የተወለዱት የኢትዮጵያ ህዝብ የዛሬ 119 አመት በአፄ ሚኒልክ መሪነት ወራሪዉን የጣሊያን ጦር አይቀጡ ቅጣት በቀጡበት አድዋ ዉስጥ ነዉ።
ወያኔ ካለፈዉ መስከረም ወር ጀምሮ ባደበዘዘዉ ቁጥር እያሸበረቀ ያሰቸገረዉን የኢትዮጵያ ታሪክ ለማቆሸሽ ጠባሳዉ ከትዉልድ ወደ ትዉልድ የሚተላለፍ የክፋት ስራ እየሰራ ነዉ። ኢትዮጵያን የመሰለ ባለታሪክ አገር ገድሎ ለሞተዉ ዘረኛ ሰዉ ትልቅ ማዕከል በህዝብ ገንዘብ የሚያሰሩት የወያኔ መሪዎች ማስቀመጫ ቦታ ጠፋ እያሉ አያሌ ብርቅ የሆኑ የኢትዮጵያ ታሪክ መጽሀፍትን ከወመዘክር አይወጡ በችርቻሮ እየሸጡ ነዉ። እነዚህ ወያኔ የሚሸጣቸዉ መጽሐፍት የተጻፉት በተለያዪ ዘመናት ወደ ኢትዮጵያ መጥተዉ በነበሩት የእንግሊዝ፤ የፈረንሳይ፤ የጣሊያን፤ የስፔንና የጀርመን የታሪክ ጸሐፊዎች ነዉ። ከሰሞኑ ከአዲስ አበባ የሚመጡ ዜናዎች እንደሚያመለክቱት ወያኔ በዉጭ አገር የታሪክ ጸሐፊዎች የተጻፉትን የታሪክ መጽሐፍትና ተጠረዝዉ የተቀመጡ ቆየት ያሉ ጋዜጣዎችን በርካሽ ዋጋ እየቸበቸቡ የግሮሰሪ ዕቃ መጠቅለያ አድርጓቸዋል።
ይህንን አሳፋሪ የሆነ የወያኔ የመጽሐፍ ሽያጭ እንደ ተራ ወንጀል የምናልፍ ኢትዮጵያዉያን ካለን እጅግ በጣም ተሳስተናል። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የሚሰሩትን ስራ አበክረዉ የሚያዉቁ ሰዎች ናቸዉ፤ እያሰሩ ያሉት ስራ ደግሞ ግልጽ ነዉ። ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የተጻፈ ታሪካችንን ብቻ ሳይሆን እያወደሙ ያሉት ባህላችንን፤ ወጋችንንና ቅርሶቻችንን ጨምር ነዉ እንዳልነበረ ያደረጉት። ለምሳሌ በብዙ የአለም አገሮች ዉስጥ ረጂም ዕድሜ ያስቆጠሩ ህንፃዎች፤ የታሪካዊ ሰዎች መኖሪያ ቤቶችና የተለያዪ የአገር ቅርሳቅርሶች ልዩ እንክብካቤ እየተደረገላቸዉ ከዘመን ወደ ዘመን እንዲተላለፉ የደረጋል። ኢትዮጵያ ወስጥ ግን ዕድሜ ለወያኔ ከፍተና ታሪካዊ እሴት ያላቸዉ ህንፃዎች በልማት ስም እንዲፈርሱ ይደረጋል። የጀግኖችን አጽም ያረፈበት የመቃብር ቦታም በግሬደር እየተደረመሰ የንግድና የችርቻሮ ቦታ ይሆናል።
ሌለዉ ወያኔ በታሪካችን ላይ የሚያደርሰዉ ጥፋት ታሪካችንን እንዳንማርና የታሪክ ተማራማሪዎቻችን በጥንታዊ ታሪካችን ላይ ምርምር እንዳያደርጉ እጅና እግራቸዉን ማሰሩ ነዉ። ለምሳሌ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ዉስጥ የሚገኛዉ የታሪክ ዲፓርትመንት የኢትዮጵያን ታሪክ ማስተማር ብቻ ሳይሆን ታሪካችንን ከተለያየ አቅጣጫ በማጥናትና ምርምር በማድረግ ለታሪካችን መበልጸግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያደርግ ተቋም ነዉ። ሆኖም ይህ በተለያዪ መንግስታት ዉስጥ ለረጂም አመታት ትልቅ ስራ ሲሰራ የቆየዉ የታሪክ ዲፓርትመንት ዛሬ አለ ተብሎ መናገር በማይቻልበት አሳዛኝ ሁኔታ ላይ ይገኛል። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ የቀድሞ ታሪካችንን እያወደመ የሚቀጥለዉን ታሪካችንን ደግሞ በራሱ አቅጣጫ እያጣመመ በመጻፍ ላይ መሆኑን ነዉ።
ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች የኢትዮጵያን ታሪክ አስመልክቶ በአንድ በኩል የኢትዮጵያ ታሪክ የተጻፈዉ በተወሰኑ ሰዎች ከአንድ አቅጣጫ ብቻ ነዉ ሲሉ በሌላ በኩል ደግሞ የረጂሙን ዘመን የአገራችን የኢትዮጵያ ታሪክ ከአንድ ሞቶ አመታ የበለጠ ዕድሜ የለዉም እያሉ በተደጋጋሚ ተናግረዋል። ዛሬ በገፍ ለጨረታ ያቀረቧቸዉ የታሪክ መጽሐፍት ቁልጭ አድርገዉ የሚናገሩት ደግሞ ታሪካችን ከ3000 ሺ አመታት በላይ መሆኑንና የተጻፈዉም በተወሰኑ ሰዎች ብቻ ሳይሆን በተለያዪ ኢትዮጵያዉያንና የዉጭ አገር ሰዎች ጭምር መሆኑንደ ነዉ። ዛሬ ወያኔ እንደ ርካሽ ዕቃ እያወጣ የሚቸበችባቸዉ መጽሀፍት ለዚህ አሳዛኝ ዕጣ የበቁት ይህንን የወያኔ አይን ያወጣ ዉሸት ስለሚያጋልጡ ነዉ።
አገራችን ኢትዮጵያን እንወዳለን የምንል ኢትዮጵያዉያን በሙሉ ይህ በአፋችን ሁሌም የምንለዉ ቃል በተግባር የምንተረጉምበት አጋጣሚ ፊት ለፊታችን ላይ ተደቅኗል። ኢትዮጵያ አንደ ገና ዳቦ ከላይና ከታች ወያኔ ባነደደዉ ረመጥ እሳት እየተለበለበች ነዉ። ይህንን እሳት ማጥፍትና አገራችንን ከወያኔ መታደግ ካለብን ግዜዉ ነገ ሳይሆን ዛሬ ነዉ።
አያሌ ኢትዮጵያዉያን የወያኔን የመጽሐፍ ሽያጭ አስመልክቶ የወሰዱትን ቆራጥና ብልህ እርምጃ ግንቦት ሰባት የፍትህ፤ የነጻነትና፤ የዲሞክራሲ ንቅናቄ እጅግ በጣም ያደንቃል። በአዲስ አበባና በአካባቢዋ የሚገኙ አያሌ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዉያን የአገርና የወገን ሃላፊነት ተሰምቷቸዉ ወያኔ ለጨረታ ያቀረበዉን መጽሐፍ በመግዛት የአገራቸዉን ታሪክ ለመታደግ ያደረጉት ጥረት በዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ አገራዊ ስራ ነዉ። አገራችን ዛሬ ባለችበት ሁኔታ ነገ አትገኝም የሚል እምነታችን የጸና ነዉና እነዚህን የገዛችኋቸዉን መጽሀፍት በጥንቃቄ በመያዝ ሀላፊነትና የአገር አደራ ለሚሰማዉ በህዝብ የተመረጠ መንግስት አንድታስረክቡ አደራ እንላችኋለን። ከአሁን በኋላም ቢሆን የወያኔን ፀረ አገርና ፀረ ህዝብ ስራ እየተከታተላችሁ እንድታከሽፉና በሚያልፈዉ ህይወታችሁ የማያልፍ ታሪክ ሰርታችሁ ወያኔን በማሰወገዱ ዘመቻ ዉስጥ ሙሉ ተሳትፎ አንድታደርጉ አገራዊ ጥሪ እናስተላለፋለን።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!

ESAT: Special Program, Free and Fair Election in Ethiopia Public Meeting in Seattle part 1 Nov 2014 | ESATTUBE

ESAT: Special Program, Free and Fair Election in Ethiopia Public Meeting in Seattle part 1 Nov 2014 | ESATTUBE

Tuesday, October 28, 2014

ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት

ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት

temesgen1
የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ቀን በዋለው ችሎት 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ ፍትህን ሲያሳትም የነበረውና ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ማስተዋል ህትመትና ማስታወቂያ በ10 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበታል፡፡
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅም 3/2007 ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አሁን የተፈረደበት በትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በአንደኛው ክስ ነው ተብሏል፡፡ የጥፋነኝነት ክሱ በተነበበት ወቅት ግን ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል ብሎ ጽፏል፡፡›› በሚል ጥፋተኝ ነው ተብሏል፡፡
አቃቢ ህግ የቅጣት ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ሆነ ጠበቃው የቅጣት ማቅለያ አላቀረቡም፡፡ በሌላ በኩል የጋዜጠኛው ጠበቃ አምሃ መኮንን ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስታውቀዋል፡፡ (ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ)

ESAT Yesamintu Engeda Ermias Legese October 2014 partr 2 & final | ESATTUBE

ESAT Yesamintu Engeda Ermias Legese October 2014 partr 2 & final | ESATTUBE

Monday, October 27, 2014

...
Ginbot 7 Lodingen Branch held a meeting Saturday. Elisabeth Tadesse, Belay Zeleke, Daniel Tesem and Michy Gizaw are among the prominent figures in the organization Lodingen. Photo: Svein Shake

- Ethiopia continues repression

LØDINGEN: - The Ethiopian government continues with clear violations of human rights, infringement of speech and freedom of the press and the right to organize and to hold open meetings.
Svein RistE-mail
 
  
Published 10/27/2014 at 24:28 Updated 27/10/2014 at 24:31


It says members of the freedom movement Ginbot 7 Lodingen Branch.
Saturday, members gathered to get information about the relationship of Ethiopia, as well as adding strategy for the continued freedom of work governed by Lodingen.
Splitter population
According Belay Zeleke has the Ethiopian government for 23 years pursued policies that have divided the population in the country.
-The Ethiopian government, led by the TPLF (Tigray People Liberation Front) continues to divide people in terms of religion, ethnicity and ethnic groups. This split creates major problems for the nation. Internal disagreements allows for TPLF to retain power, maintains Zeleke.
During Saturday's meeting in Lodingen it was claimed that the government of Ethiopia oppress the population by introducing a number of restrictions.
-Etiopiske Government continues with very severe restrictions on the most basic human rights, freedom of expression, freedom of association, and freedom to hold meetings. This is why Ethiopians - both at home and outside - protests and campaigning against the incumbent government, says Michy Gizaw.
Arbitrary detention
Arbitrary detention and abduction, according to Elisabeth Tadesse methods the leading party in Ethiopia uses.
-In Advance of the last election made it the leading party many difficulties and much unrest. Among other things, by arresting journalists and political activists. Several were also forced to leave the country. People who use facebook, blogs and other social media to show the world the true face of the government also risk imprisonment and persecution, said Tadesse.
Pursued also abroad
During Saturday's meeting in Lodingen revealed that there currently is no freedom of expression in Ethiopia.
Media is under great pressure because very few journalists left in the country.
-They Are either imprisoned or forced to leave the country. Ethiopian authorities also go to other countries, where the outright kidnapping political activists. This has happened countless times, says Daniel Tesem, and cites a couple of examples.
-Okello Akuay Ochalla is from Ethiopia, but has Norwegian citizenship. He traveled earlier this year to Sudan. He was picked up by Ethiopian authorities, led over the border and imprisoned. He may face the death penalty for his work in a political organization, says Tesem.
-Also Andargachew Tsigas, with English citizenship and one of the leaders of Ginbot 7, was kidnapped from Yemen by Ethiopian security forces and is currently in prison in Ethiopia. Neither Ochalla or TSIG is criminal. The only political activists who want a democratic Ethiopia with a good judiciary, freedom of expression and human rights in general, concludes Daniel Tesem.
Ginbot 7 Lodingen Branch wants to focus on human rights violations and abuses of political opponents in Ethiopia, as well as being a mouthpiece for the millions of 

Ethiopia court sentenced journalist Temesgen Desalegn to three years in jail | Zehabesha – Latest Ethiopian News Provider

Ethiopia court sentenced journalist Temesgen Desalegn to three years in jail | Zehabesha – Latest Ethiopian News Provider

Habtamu Ayalew at Addis Ababa Protest - Must Watch

ሀገር ማለት ፣በሀብታሙ አያሌው

ESAT Efeta Oct 25 2014 | ESATTUBE

ESAT Efeta Oct 25 2014 | ESATTUBE

Thursday, September 18, 2014

UN experts urge Ethiopia to stop using anti-terrorism legislation to curb human rights

UN experts urge Ethiopia to stop using anti-terrorism legislation to curb human rights

UN Experts Urge Ethiopia To Stop Using Anti-Terrorism Legislation To Curb Human Rights

Sep182014
ethiopian demo 1GENEVA – A group of United Nations human rights experts* today urged the Government ofEthiopia to stop misusing anti-terrorism legislation to curb freedoms of expression and association in the country, amid reports that people continue to be detained arbitrarily.
The experts’ call comes on the eve of the consideration by Ethiopia of a series of recommendations made earlier this year by members of the Human Rights Council in a process known as theUniversal Periodic Review and which applies equally to all 193 UN Members States. These recommendations are aimed at improving the protection and promotion of human rights in the country, including in the context of counter-terrorism measures.
“Two years after we first raised the alarm, we are still receiving numerous reports on how the anti-terrorism law is being used to target journalists, bloggers, human rights defenders and opposition politicians in Ethiopia,” the experts said. “Torture and inhuman treatment in detention are gross violations of fundamental human rights.”
“Confronting terrorism is important, but it has to be done in adherence to international human rights to be effective,” the independent experts stressed. “Anti-terrorism provisions need to be clearly defined in Ethiopian criminal law, and they must not be abused.”
The experts have repeatedly highlighted issues such as unfair trials, with defendants often having no access to a lawyer. “The right to a fair trial, the right to freedom of opinion and expression, and the right to freedom of association continue to be violated by the application of the anti-terrorism law,” they warned.
“We call upon the Government of Ethiopia to free all persons detained arbitrarily under the pretext of countering terrorism,” the experts said.  “Let journalists, human rights defenders, political opponents and religious leaders carry out their legitimate work without fear of intimidation and incarceration.”
The human rights experts reiterated their call on the Ethiopian authorities to respect individuals’ fundamental rights and to apply anti-terrorism legislation cautiously and in accordance with Ethiopia’s international human rights obligations.
“We also urge the Government of Ethiopia to respond positively to the outstanding request to visit by the Special Rapporteurs on freedom of peaceful assembly and association, on torture and other cruel, inhuman or degrading treatment or punishment and on the situation of human rights defenders,” they concluded.
(*) The experts:  Special Rapporteur on the promotion and protection of human rights and fundamental freedoms while countering terrorism, Ben Emmerson; Special Rapporteur on the rights to freedom of peaceful assembly and of association, Maina Kiai; Special Rapporteur on the promotion and protection of the right to freedom of opinion and expression, David Kaye; Special Rapporteur on the situation of human rights defenders, Michel Forst; Special Rapporteur on the Independence of Judges and Lawyers, Gabriela Knaul; Special Rapporteur on torture and other cruel, inhuman or degrading treatment or punishment, Juan Méndez.

Wednesday, July 2, 2014

የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ታገቱ ለኢህአዴግ ተላልፈው ከተሰጡ ድርጅቱ የበቀል እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ታገቱ

ለኢህአዴግ ተላልፈው ከተሰጡ ድርጅቱ የበቀል እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ
andargachew
ከግንቦት 7 የተሰጠው መግለጫ ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ
ሰኔ 23 ቀን 2006 .
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።
ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።
መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።
በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።
በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
መግለጫው በንቅናቄው ድረገጽ እዚህ ላይ ይገኛል

“የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም” – ግንቦት 7 (መግለጫ በአንዳርጋቸው ዙሪያ) | Zehabesha Amharic

“የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም” – ግንቦት 7 (መግለጫ በአንዳርጋቸው ዙሪያ) | Zehabesha Amharic

ከግንቦት 7 አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ
ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም
የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።
andaregachew-tsege-300x498
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።
ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።
መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።
በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።
በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

Monday, May 19, 2014

“ደረቅ ራዕይ” – “ደረቅ ትግል” | Zehabesha Amharic

“ደረቅ ራዕይ” – “ደረቅ ትግል” | Zehabesha Amharic

"ደረቅ ራዕይ" - "ደረቅ ትግል"
ሚኪያስ ሙሉጌታ ግዛው ከኖርዌ
ሠማይ ጠቅስ ሕንፃዎች ተደርድረዋል ይባላል። ሠፊው ጎዳና የሠማዩን አድማስ አቋርጧል ይባላል። ወንዙ
ተገድቦ ውሃው ተንጣሎ ተኝቷል ይባላል። ማዶ ከተራራው ሥር ዘመናዊ የእርሻ ልማት ይታያል ይባላል።
የእድገቱ አሃዝ ጨምሮ የሕዝቡ ኑሮ መሻሻሉን የሚዘግብ ዶኩሜንተሪ ፊልም በቴሌቪዥን ይታያል። የአቶ
መለስ ራዕይ ሠምሯል ማለት ይሆን? - ግናስ ሀገሬ ኢትዮጵያ ምን ነካት? – ምነው ኩርምት አለች? – ምነው
ገጿ ደበዘዘ?
የአቶ መለስ ራዕይ ሉዓላዊነቷን ያስደፈረ፣ ኅልውናዋን የተፈታተነ፣ ታሪኳን ያንቋሸሸ "ደረቅ ራዕይ" ስለነበር
ነዋ። እምዪ ኢትዮጵያ ምነው ታድያ ኩርምት አትል? ምነው ገጿ አይደበዝዝ`? ራዕዩ የሕንድና የአረብ
ከበርቴዎችን ያስፈነጠዘ፣ ሼሁንና ሎሌዎቹን ያወፈረ፣ የቅኝ ገዢዎችን ምኞት ያሳካ፣ በርካታ ቀን የሰጣቸውን
ባለስልጣናትና ዘመዶቻቸውን ያባለገ ራዕይ ነበር። በአለም ባንክ ርዳታ የተነጠፈው ጎዳና ረጅም - ግን ደረቅ
የሙስናውንና የኤፈርቱን የዘረፋ ሸቀጥ በተሸከሙ ከባድ መኪኖች የተጨናነቀ ጎዳና ነው። በየመስኩ
የተንጣለሉት ሌብነትና ጉቦ ወለድ ፋብሪካዎቹ የሕዝቡን ኑሮ አላሽቀውታል። ራዕዩ ሃይማኖትን ሳይቀር
የተፈታተነ ሕዝብን ያጠወለገ የክፋት ምንጭ ነበር። ዛሬ ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ቀድሞ ተንሰራፍቶ የነበረው
ሙስና ገሃድ ወጥቶ ሙስናውያኑን እያባረረ ነው። በቅርቡ በኦሮምያና ትግራይ ክልሎች ባሉ ትልቁ የሙስና
ዋሻ የመሸጉ ሁሉ ሙቅ ውሃ እንደተደፋባቸው አይጦች ይራወጣሉ። የስባዓዊ መብት ጥሰቱ ይቁም (Stop
human rights violation)፣ አምባገነንነት ይውደም (Down with Dictatorship)፣ ሙስናው ያብቃ (Stop
Corruption)፣ የሚሉ ሰላማዊ መፈክሮች ይዘን ስለወጣን ለስደት የዳረጉን ከቀበሌ እስከ መንግስት አመራር
ያሉ ሁሉ ነገ ተጠያቂዎች ናቸው።
በእርግጥ ሙስናው ያደለባቸው አምባገነኖች ደረቅ ተቃውሞን አይፈሩም። ደረቅ ከደረቅ ቢጋጭ ለውጥ
እንደማይመጣ ተንኮሉን ጫካ እያሉ አውጠንጥነውታል። አምባገነኖቹ ደረቅ ወሬን፣ ደረቅ ጽሁፍን፣ ደረቅ
ጩኸትን፣ ደረቅ አመጽን አይፈሩም። ደረቅና ውሸት ጋጋታዎች የእድሜአቸው ማራዘምያ ኪኒኖች ናቸው።
ወያኔነዎቹ በበርሃ ላይ ድንገት ፍልቅ እንደምትለው ምንጭ ርጥብ ነገርን ከተመለከቱ ነው ክው የሚሉት።
ታድያ መልሰው እስኪያደርቋት ድረስ እንቅልፍ አይወስዳቸውም። ዓይነተኛ ባህርያቸው ይህ ነው። ወያኔዎች
እስክንድር ነጋንና አንዷለምን እንደ ጦር ይፈራሉ። ወደፊት ሌላ እስክንድርና አንዷለም ዓይነቶች
እንዳያብቡም ነው ዛሬ በሰማያዊ፣ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ ከፍተኛ ወከባ የሚያደርጉት። አቶ
መለስን ትንሿ የእስክንድር የብዕር ጠብታ ለፍርሀቱ ስትዳርጋቸው - የአበበ ገላው ድምጽ ደግሞ ኃይል
አግኝቶ አንገታቸውን አስደፍቷቸው ነበር።
ዛሬ ሃገሬን ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን የቀሰፈው ትልቁ በሽታ ፍርሃቱ እንጂ የኢሕአዲግ ብርቱነት አይደለም።
ደረቅ ትግሉ ተስፋ አስቆርጦ አድርባይነትን አስፋፍቷል። ድርቀቱ የተግባር ብኩንነቱን አስፋፍቶ "እስኪ
ልኑርበት" የሚሉ ግለሰቦችን አብዝቷል። ድርቀቱ "ቤቴን ልስራበት - ልጆቼን ላሳድግበት" የሚሉ ፈሪዎችን
አበራክቷል። እምነት ደርቃ ቤተክርስትያን ሂያጁ የትለሌ አስኪሆን ድረስ "ደረቅ ትግሉ" የአስመሳዮች ምሽግ
ሆኗል። ጸሎቶች ደረቅ ጸሎቶች ሆነዋል። ድርቀቱ የሕዝቡን አንድነትም ሆነ የተቃውሚውን የፖለቲካ ስልት
አወላግዷል። ታድያ ለዚህ ሁሉ ከንቱነት የዳረገንን አዚም ሳጤን – "በርግጥ አቶ መለስ ለካ - የደረቁ ምጣኔ
ኃብት ፈላስፋ፣ የአፈናና ስውር ግድያ መሃንዲስ፣ የታላቁ ሤራና የደረቁ ትግል ስትራቴጂስት፣ የክፉ
አደረጃጀት ስልት ቀያሽና ሕዝብ ከሕዝብ - ዘር ከዘር እሚናከስበትን መላ ጠንሳሽ፣ የመሃይማንና የደናቁርት
ስብስብ መሪና - የኃጢዓት ሥራ ዋና ተዋናይ ነበሩ" - ለማለት እደፍራለሁኝ። ብቻ ፍርዱን ለእግዚአብሔር
እንተወው።
የሚያሳዝነው ታድያ እስካሁን ድረስ በአቶ መለስ መተት ለተቀሰፈው የውስጡም የውጭውም ደረቅ ትግል
ማርጠብያ መድሃኒት አለመገኘቱ ነው። መፈክሮቻችን፣ ሰልፎቻችን፣ ስብሰባዎቻችን፣ ጽሑፎቻችን የታንክ
ጥይት ቢሆኑ ኖሮ የሕወሀት ዘመን አጭር በሆነ ነበር። እንደተዋጊ ጄቶች የፈጠኑት ድኅረ ገጾች፣ ጋዜጦችና
መጽሄቶች ቦንብ ተሸካሚዎች ቢሆኑ ኖሮ ሕወሀትና ሻዕቢያ መቀመቅ ወርደው ሕዝቦች ነጻ በወጡ ነበር።
በገቡ በጥቂት ቀናት መወገድ ስለነበረባቸው ኢሕአዲጋውያን በማውሳት ሕዝቡ - "ሳንፈልጋቸው ሀያ
ሞላቸው" – በማለት ብሶቱን አች አምና በታላቁ ሩጫ ወቅት አሰምቷል። ትግሉ እጅግ ለመዘግየቱ ከዚህ ሌላ
ምን ማስረጃ አለ?
የአቶ መለስ መንፈስ በተቃዋሚው ጎራ ሳይቀር ሰርጎ ገብቶ ተግባር በሌለው ምላሳቸው ሰብዓዊ መብት
ተገፈፈ፣ ምርጫው ተዛባ፣ ሙስና ተስፋፋ፣ ዲሞክራሲ የለም - እያሉ የሚያስተጋቡ ልሳናቸው የኢትዮጵያን
ክብር የማያውጅ ደረቅ አስመሳይ ተባባሪዎችን ሳይቀር አፋፍቷል። ባጠቃላይ "ደረቅ ትግሉ" የኢትዮጵያ
የቀድሞ ክብሯና ገናናነትዋ ዳግም እንዳይመለስ ለሚፈልጉት ምዕራብያውያን እፎይታ፣ ለኢሕአዲጎቹ እድሜ
ማራዘምያ ኪኒን፣ ለሻዕቢያ - ለኦነግና ለአልሻባብ ጊዜ መግዢያ አሞሌ ጨው እንዲሁም በዝርፊያና በወንጀል
ተጠያቂ ለሆኑት ግለሰቦች ሽፋን ሠጪ ተኩስ ከመሆን በቀር ለኢትዮጵያና ለሕዝቦቿ አፋጣኝ መድህን መሆን
አልቻለም፣።
ልብ በሉ! ኢሕአዲጎቹን ማስወገድ ያለብን የቅኝ ገዢዎች ተባባሪዎች፣ ለሀገሪቱ ሉዓላዊነት፣ ክብርና ታሪክ
ፈጽሞ የማይጨነቁ፣ ሃገሪቱን ወደብ አልባ ያደረጉ፣ ኃይማኖትን የበከሉ፣ ሕዝቡን ለ"ስደት ሞት"ና ለ"ዳግም
ክፉ" ቀን የዳረጉ ሰው መሰል ጨካኝ አራዊቶች ስለሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በኢንተርኔት፣ ፓልቶክ፣ ሬድዮና
ቴሌቪዥን በሚተላለፍ "ደረቅ ትግል" ብቻ አይሞከርም። ዛሬ በአቶ መለስ የሙት መንፈስ ምስል እየተመራ
በመበታተኑ ጣዕረ ሞት የሚያቃስተውን ኢሕአዲግ ገፍትረን መጣል ካልቻልን ነገ አገግሞ ለሌላ መቅሰፍት
ይዳርገናል። እንዲህ ተበታትነን፣ መስዋዕትነት የከፈሉትን ጀግኖች ገለል እያደረግን፣ ለወንጀለኞችና ለበታኞች
ፍሪዳ እያረድን፣ የጓደኝነቱን፣ የአበልጅነቱን፣ የሚዜነቱን "ስውር አብዮት" በየመሸታው እያጠናከርን - በደረቅ
ትግሉ ብቻ ተቃውሞን ከቀጠልን የሀገሪቱ መጪ እድል መገነጣጠል፣ መፈረካከስ - የሕዝቡ ዕጣ ደግሞ
መራብ መታረዝ ብሎም - የ"ስደትን ሞት" - እንደ ብቸኛ አማራጭ አድርጎ መቀበል ብቻ ነው።
ወያኔን ለማስወገድ መፍትሄው አንድ ብቻ ነው። መፍትሄው የመንፈስ ፅናት ነው። እንደ አለፈው ትውልድ
የጠላት ፈረስና ሰረገላ ማኅተማቸውን ሳያላላ፣ በእግዚአብሄር ኃይል ራሳቸውን አበርትተው፣ በባህሩ በደረቅ
መሬት፣ በሸለቆና በተራራው ተሰማርተው የሃገሬን ቁስለቷን እንደ ሻሩላት ጀግኖች ምሳሌ ለመሆን አስቀድሞ
የፅናቱ ቅባ ቅዱስ እንዲነካን በይቅር ባይነትና ፍቅር ዳግም መደራጀት ይኖርብናል። ፅናት አቋምን
ትወልዳለች። ውጤት የምናመጣው የሕዝብ ወገን የሆንን ሁሉ በሕብረት ተደራጅተን እንደ አንድ ሰው ሆነን
ስንታገል ብቻ ነው።
አለበለዝያማ ጽናትን የሚያጎለብተውን፣ የጀግኖቹን ፈለግ መከተሉን ትተን፣ ጋጋታና አጀብ ስናበጃጅ ዘመኑ
በከንቱ እንዳያልፍ እንጠንቀቅ። የመስመር ልዩነት የሌላቸው ፖለቲካ ፓርቲዎች በቶሎ ወደ አንድነቱ
መምጣት አለባቸው። ለሃገሪቱ ርጥብ ራዕይ ያላቸው ድርጅቶች ሁሉ መቀራረብ አለባቸው። ኢትዮጵያ
የምታገግመው ከትግሉ ሜዳ በተለያዩ ምክንያት የራቁትን ጀግኖቿን በፍቅር ተማጽኖ ትግሉን እንደገና
እንዲቀላቀሉ ሲደረግ ነው። ማዕከላችን ኢትዮጵያ ነች። ሁላችንም ለኢትዮጵያ እናስባለን። ልዩነታችን
ውበታችን ነው። አንድነታችን አምባገነንነትን ያንበረክካል። ሙስናን ያጠፋል። ኢትዮጵያ የሰው ልጆች መብት
የማይረገጥባት ሀገር ትሆናለች።
አምላክ ኢትዮጵያን ይጠብቃት።
አድራሻዬ michyas.ethio@yahoo.com ነው።

Thursday, May 1, 2014

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!


ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲንቅናቄ፣ ዘረኛው ወያኔ በኦሮሚያ ሕዝብና ወጣቶች ላይ እያካሄደው ያለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ፣ እስርና አፈናን በጥብቅ ይቃወማል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን ያስገነዝባል።
የአሮሚያ ወጣቶች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም የድሀ ገበሬዎች መፈናቀልን መቃወማቸው ፍትሀዊ ነው። የወያኔ “ማስተር ፕላኖች” የወያኔ የዘረፋ እቅዶች መሆናቸው በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው። ነዋሪዎቹን ያላማከረ፣ ግንባር ቀደም ባለጉዳዮችን ባለቤት ያላደረገ፣ የሕዝብ ይሁንታ ያላገኘ ማስተር ፕላን ተፈፃሚ ማድረግ አይቻልም።
ወያኔ ኦሮሚያን ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያ በምስለኔዎቹ አማካይነት እየገዛ የኢትዮጵያን ውድ ልጆች በራሳቸው ጉዳይ ባይተዋር አድርጓቸዋል። ኦህዴድ በወያኔ ቅጥረኛነት የኦሮሚያ ወጣቶችን በማስጨፍጨፍ ላይ ያለ እኩይ የአድርባዮች ስብስብ ነው።  ወጣቶች የተቃወሙት ይህንን ነው።እነዚህ ወጣቶች በአካባቢያቸው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባቸዋል። ድምፃቸው ሊሰማ ይገባል። የሌላው አካባቢም ወጣት የኦሮሚያ ገበሬ መፈናቀል ያገባዋል። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በሚደረግ ጉዳይ ሁሉ ያገባናል። በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወያኔ የራሱን እቅድ እንዲጭንብን አንፈልግም።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ አድርጎ እንዲወስድ ጥሪ ያደርጋል።  በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል የተጀመረው መፈናቀል ዛሬ አዲስ አበባ አጎራባች ከተሞች ደርሷል። በአምቦ ይህንን የተቃወሙ ወጣቶች በግፍ ተጨፍጭፈዋል፤ በሌሎች ቦታዎችም ላይ ግድያውና እስሩ በርትቷል። ወጣቱ  የጥይት እራት ሆኖ እስኪያልቅ መጠበቅ አንችልም፤ ሁሉም ትግሉን ይቀላቀል።
የወያኔ የጥቃት ሰለባ የሆኑት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይን ያነሱ ወጣቶች ብቻ  አይደሉም። በአንድ ወይም በሌላ መንገድ የወያኔን አምባገንነት የተቃወሙ በሙሉ የጥቃቱ ሰላባዎች ናቸው። ለሰልፍ ቅስቀሳ አደረጋችሁ በሚል የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ሰልፉ ተደርጎ  ካለቀ በኋላም አልተፈቱም።  ይህ ሰቆቃ ማብቃት አለበት።
ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

Ethiopian Security Forces opened fired and killed 30 people | Zehabesha – Latest Ethiopian News Provider

Ethiopian Security Forces opened fired and killed 30 people | Zehabesha – Latest Ethiopian News Provider

Friday, April 4, 2014

ትንሽ ምላጭ አገር ትላጭ!

መጠላለፍ ወደየትኛው ገደል እየመራን ነው?
fire1
የአዲስ አበባን መኪናዎች በተለይም በጫት የሚሽከረከሩት ታክሲዎችን በማንኛውም መስቀልኛ መንገድ ላይ ለአምስት ደቂቃ ቆሞ የተመለከተ ሰው በቀላሉ እንደሚረዳው “እኔ ካላለፍሁ ማንም አያልፍም!” በሚል መመሪያ መኪናዎቹ ተቆላልፈው እንዲቆሙ ማድረግ ነው፤ እንደሚመስለኝ የአባቶቻችንን ዕዳ እየከፈልን ነው፤ ዱሮ በደጉ ዘመን ሁለት ኢትዮጵያውያን መስቀልኛ መንገድ ላይ ሲገናኙ አንተ-እለፍ አንተ-እለፍ እየተባባሉ የሰማዕታቱንና የቅዱሳኑን ስም እየጠሩ ይገባበዙ ነበር! ይህ ባህል በጠንካራ የሥልጣኔ ላጲስ ተደምስሶ ጠፍቶ በምትኩ እኔ ካላለፍሁ ማንም አያልፍም መንገዱን ሁሉ መቆላለፍ አዲስ የመጠላለፍ ባህል እየተተከለ ነው፤ የመጠላለፍ ባህል የሚታየው በባቡር መንገዶች ላይ ብቻ አይደለም፤ በብዙ ነገር መጠላለፍ ባህል እየሆነ ነው! የዚህ ዝንባሌ መጨረሻው አሸናፊ የሌለበት ሙሉ ጥፋት ነው።
በመንገዶች ላይ ጥቂት በጫት የሚነዱ መኪናዎች በመቶ የሚቆጠሩ መኪናዎች እንዳይንቀሳቀሱ ለማድረግ ይችላሉ፤ ሲያደርጉም በየቀኑ እየታየ ነው፤ በማኅበረሰባዊና በፖሊቲካ ግንኙነትም አንድ ሰው የሚዘራው መርዝ የጊዜው ሁኔታ በሚፈቅድለት ፍጥነት የማኅበረሰቡን አባላት ያዳርሳል፤ እንቆቅልሹ እንደሚለው ትንሽ ምላጭ አገር ትላጭ! ማለት መርዝ፣ እሳት፣ ተላላፊ በሽታ በሕዝቡ ላይ ማሰራጨት ከአምስትና ከአሥር ዓመታት በኋላ ውጤቱ ምን እንደሚሆን መገመት አያቅትም።
ድብብቆሽ አይጠቅምም፤ሁለት ነገሮችን በግልጽ ማውጣት አለብን፤አንደኛ በአሜሪካና በአውሮፓ መሽጎ ፍርሃቱንና ሽቁጥቁጥነቱን ለመሸሸግ መርዙን በኢትዮጵያውያን ላይ የሚረጨው ለምንድን ነው? አገዛዙ ይህንን የሚያደርግበት ምክንያት ግልጽ ነው፤ ከፋፍሎ የመግዛት ዘዴ ነው፤ ከአገዛዙ ጋር በሚደረግ ትግል ከታች ሆነው ከሥልጣን ውጭ የሆኑ ዜጎች በሥልጣን ላይ ከተቀመጡት ጋር እየተቆራቆዙና እየተጋጩ ናቸው፤ ይህንን እኔ የላይና-የታች ግጭት (vertical conflict) የምለው ነው፤ ከወያኔ/ኢሕአዴግ ጋር የሚደረገው ትግል ይህ ነው፤ ይህንን ለማክሸፍ ወያኔ/ኢሕአዴግ ትግሉን ከላይና-ታች አውጥቶ ወደጎን-ለጎን ግጭት (horizontal conflict) ሊለውጠው ይፈልጋል፤ ከወያኔ/ኢሕአዴግም ውጭ በጎሠኛነትና በሃይማኖት አክራሪነት የደነዘዙ ሰዎችም ትግሉን ጎን-ለጎን ሊያደርጉት እየሞከሩ ናቸው።
የፖሊቲካ ትግልን የሚመሩ ሰዎች በጎሠኛነትና በሃይማኖት አክራሪነት ስሜት እየተሳቡ ትግሉን የላይና-የታችነቱን ጠብቀው በተደራቢነት የጎን-ለጎን ትግሉን ይጨምሩበታል፤ ይህ ሲሆን ሀሳብ፣ ጉልበትና ሀብት ይከፋፈላል፤ ይበታተናል፤ ወደዓላማ ለመድረስም ያስቸግራል፤ ወያኔ ወደመጨረሻው ላይ ኢሕአዴግ ብሎ የሰየመውን ቀፎ አስቲፈጥር ድረስ በስሙ ውስጥ ኢትዮጵያን የሚያነሣ ነገር አልነበረውም፤ ወያኔን ለድል ያበቃው የማታለያ ስሙ እንደሆነ በበኩሌ አልጠራጠርም፤ ከሃያ ሁለት ዓመታት የጎሣ ሥርዓት በኋላ ኢትዮጵያ ቆስላለች እንጂ አልሞተችም፤ የአሐዝ ማስረጃ ለማቅረብ ባልችልም በብዙ ጎሣዎች መሀከል ጋብቻ እንደዱሮው እየቀጠለ ነው፤ ይህንን የቆየ የዝምድና ሰንሰለት ለመበጠስ የሚጥሩም አሉ።
ኒው ዮርክ ተቀምጦ ትኩስ ውሻ (ሆት ዶግ!) እየበላ ለእስላም ኦሮሞዎች የመገዳደያ መመሪያ የሚሰጥ ሰው የመንፈስ ጤንነቱን እጠራጠራለሁ፤ ይህንን የኒው ዮርክ ቀረርቶ ተከትሎ ሌላ የመጠላለፍ አዋጅ ሰማን፤ ቴዎድሮስ ካሣሁን ለአጼ ምኒልክ ስለዘፈነ ከበዴሌ ቢራ ፋብሪካ ጋር ለማስታወቂያ የገባው ውል ሥራ ላይ ከዋለ የበዴሌን ቢራ አንጠጣም ተባለና ማስታወቂያው ተሰረዘ ይመስለኛል፤ ማን እንዳሸነፈ ወደፊት ጊዜ ይነግረናል፤ አሁን ደግሞ ሌላ ማዘዣ ሰማሁ፤ “የስ” በሚለው ውሀ ጠርሙስ ላይ እንስራ የተሸከመችው ኮረዳ መስቀል አድርጋ ነበር፤ ልጅቱ ከነመስቀልዋ የምትታይበትን ውሀ እስላሞች አንገዛም ስላሉ ነጋዴዎቹ መስቀሉን አወለቁባት! ይህንን ማዘዣ ላወጣው አክራሪ እስላም ወረባቦ ቅዳሜ ገበያ ሄዶ እንዲጎበኝ አሳስበዋለሁ፤ ዛሬ ተለውጦ እንደሆነ አላውቅም እንጂ እኔ ብዙ ጊዜ ተመላልሼ እንዳየሁት የወረባቦ ኮረዶች ሁሉ ትልልቅ መስቀል በአንገታቸው ላይ ይታይ ነበር፤ መስቀል የእምነት መግለጫ ይሆናል፤ አያጠራጥርም፤ ግን መስቀል ጌጥም ይሆናል! መስቀል የናዚ ምልክትም ሆኖ ነበር! ለማናቸውም የዚህ ዓይነቱን መጠላለፊያ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የሚገምዱ ሰዎች ዓላማቸው ማንንም ለመጥቀም ሳይሆን ፍቅርንና ሰላምን ለማደፍረስ ነው፤ የኢየሱስ ክርስቶስ መሠረታዊ ትምህርት ክፉን በክፉ አትመልሱ ነውና ለተበጠሰው መስቀል አጸፋውን ለመመለስ ማሰብ አይገባም።
ከኒው ዮርክ የተሰማው ቀረርቶም ሆነ የመስቀል ማስወለቁ ጉዳይ የተከሰተበትን ጊዜ ልብ ልንለው ይገባል፤ እስላሞች ስለነጻነት የሚያደርጉት ንቅናቄ በጣም እየጋለ በመሄድ ላይ እያለ ክርስቲያኖችም የዜግነት ግዳጃቸው አድርገውት ድጋፋቸውን በሚሰጡበት ጊዜ ነበር፤ ይህ መሆኑ ጥርጣሬን ይጋብዛል፤ የገጠመውን የእስላሞችና የክርስቲያኖች ሰልፍ በማደፍረስ ወይም በመክፈል የሚጠቀም ማን ነው? የሚጎዳውስ ማን ነው? ሁሉም የትግል አጋፋሪዎች ለዚህ ጉዳይ የሚያስፈልገውን ክብደት ቢሰጡት ትግሉ በጎን-ለጎን እንዳይሄድና እንዳይዳከም ይረዳል፤ ከዚያም በላይ አክራሪነት የሚባለውና የሚያስከትለውም ሽብርተኛነት የሚመጣው እንዲህ እያለ ነው፤ እግዚአብሔር ከዚያ ያውጣን!
ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
መጋቢት 2006