Wednesday, August 31, 2016

ሰበር ዜና የትግራይ ወጣቶች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ትእዛዝ ተሰጠ

ሰበር ዜና
የትግራይ ወጣቶች በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ትእዛዝ ተሰጠ 
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ አባይ ወልዱ እና ከፍተኛ የህወሓት ሹማምንቶች እምነት የሚጣልባቸው የፓርቲው ወጣት አባላትን ስብስበው ጠንካራ ትእዛዝ አስተላለፉ::
"በእናቶቾቻችሁ፥ በአባቶቻችሁ፥ በእህት፥ ወንድሞቻችሁ ደምና አጥንት ማንነታቸሁ ተከብሯል:: ደርግ ወንበዴ እያለ ሲጨፈጭፈን መስዋዕትነት ከፍለን በሰላም የምትኖሩበት፥ የምትማሩበት፥ የምትሰሩበት እና በክብር ወጥታችሁ የምትገቡበት ናጽነት አግኝተናል::
አሁን ግን የጥፋት ኃይሎች በሻእቢያ እና ግብጽ በመታገዝ ደርግን መልሰው ሊያመጡብን ትግራዋይ ላይ ግልጽ ጦርነት አውጀዋል:: ስለዚህ ይህን የመመከት ኃላፊነት በእናንተ ወጣቶች ላይ ተጥሏል::
ወላጆቻችሁ ትምክህተኞችን ጠባቦችን ደምስሰው በኢትዮጵያ ሰላም ልማት እና ዲሞክራሲ አንዳሰፈኑት ሁሉ እናንተም አኩሪውን ታሪክ የመድገም ግዴታ አለባችሁ:: አለበለዚያ የተጋሩ ህልውና አደጋ ላይ ይወድቃል ብሎም ከላይ የሻእቢያ ከታች የትምክህተኞች ጥቃት መፈንጫ ሆኖ እንደ ሕዝብ የመቀጠል እድል የማይታሰብ ይሆናል:: በተለይ በ አሁኑ ሰዓት በአማራ ክልል ሁከት በተጋሩ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ይህንኑ ያመላክታል::
ይህን አውቃችሁ ህወሓትንም ትግራይንም ከጥፋት በማዳን የተጋሩን ቀጣይነት አረጋገጡ:: ባለራዕዩ መሪያችን መለስ ዜናዊ የጣለብንን አደራ እንወጣ::በእናንተ ፍጹም እምነት አለን::"
በትላንትናው ዕለት ገዢው ስርዓት በግልጽ አማራ ክልል በወታደራዊ እዝ ስር እንደሚሆን በመግለፅ በከባድ መሳሪያ የታገዘ መከላከያ ሰራዊት ወደስፍራው አሰማርቷል ::
ኦሮሚያ ክልል አብዛኛው ክፍሉ በህወሓት ሰራዊት የታጠረ መሆኑ ይታወቃል::
የህወሓት ትእዛዝ ፈጻሚ የሆነው ብአዴን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አያፈነገጠ በመምጣቱ እና ሕዝባዊ ንቅናቄው ላይ የሚጠበቀውን የኃይል እርምጃ ባለመወሰዱ በኦህዴድ አመራሮች ላይ እንደደረሰው የመባረር እጣ የሚገጥማቸው ባለስልጣናት ይኖራሉ:: በተጨማሪ የብአዴን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ በህወሀት ቁጥጥር ስር ይሆናል::

Sunday, August 21, 2016

ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ዋልድባ ፡ ከእሾህ የተጠጉ አጋሞች ከ ሚክያስ ግዛው

                            ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ ዋልድባ ፡ ከእሾህ የተጠጉ አጋሞች
                                                 ከ ሚክያስ ግዛው
የቀድሞው የኢትዮጵያ ንጉሥ የነበሩትን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ፎቶግራፎችና ቪዲዮዎች ማየት እወዳለሁ። በተለያዩ አጋጣሚዎች ከልጅ ልጆቻቸው ጋር አብረው ሆነው ፎቶግራፍ ተነስተዋል። ልጆቹ አያታቸው ንጝር ሲያደርጉ ያዳምጣሉ፣ ጉብኝት ሲያደርጉም ያያሉ። ገና ከጨቅላነታቸው የሃገር መሪን ሥራና ኃላፊነት እየተገነዘቡ ያድጋሉ። እርሳቸው ጃንሆይም ቢሆኑ አጼ ሚኒሊክ አጠገብ ፎቶግራፍ ተነስተው እንደነበር አይቻለሁ። አጼ ሚኒልክም አጼ ቴዎድርስን እየተከተሉ አስተዳደርና ፍርድ ተመልክተዋል። ጥሩ ነው፣ መጥፎ ድርጊት አይደለም። እኛም እናትና አባታችንን እየተመለከትን የነሱን ባህርይ ቀድተናል፣ የነሱን ሥብዕና ተላብሰናል። የጃንሆይን ፎቶግራፎች ግን ስመለከት አንድ ነገር ወደ ውስጤ ይወረወራል። ጃንሆይ እነዛን የሚሳሱላቸው እምቦቅቅላዎች ነገ ስደተኞች እንደሚሆኑ ግን ከቶ ያሰቡ አይመስለኝም። እርሳቸው ከአጼ ሚኒልክ የተረከቡትን ሥርዓት እንዲህ በቀላሉ ለልጅ ልጆቻቸው የሚያስረክቡ መስሏቸው ነበር። የአድዋው ጀግና የራስ መኮንን ልጅ፣ ያንን የአጼ ሚኒልክን ስብዕና በዓይን የቃኙ፣ አስተዋይና ብርቱው ጃንሆይ እንዴት የወደፊቱን መተንበይ እንዳልቻሉ ሳስበው ይገርመኛል። የጃንሆይ መንግሥት ሲገረሰስ ልጆቻቸው፣የልጅ ልጆቻቸው ስደተኞችና እስረኞች ሆኑ። ከጃንሆይ ሃገሪቱን የተረከቡት ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ለፎቶግራፍ ብዙም ጊዜ አልነበራቸውም። የእፎይታ ጊዜ ስላልነበራቸው ልጆቹን ፎቶግራፍም አለስነሱም። ባለቤታቸውም ብዙ አይታወቁም። ቢሆንም ግን ተሰደዱ። ከደርግ ሥርዓቱን የተረከቡት አቶ መለስ ዜናዊ ግን ከሁለቱ መሪዎች ይልቅ ጮሌ ነበሩ። ለልጆቻቸው ፎቶግራፍ አይደለም የሚያወርሱት። ለልጆቻቸው ገንዘብ ለማውረስ ነው የማኦ ሴቱንግን መጽሃፍ ተንተርሰው ያድሩ የነበረው። የማኦ ሴቱንግ መጽሃፍ ስለገንዘብ አያወራም ግን ሥልጣን ከጠመንጃ አፈሙዝ መወለዱን ያብራራል። የደደቢቱ ፈላስፋ አቶ መለስ ዜናዊም ገንዘብ ከጠመንጃ አፈሙዝ ይወለዳልዕ ሲሉ የማኦን ሃሳብ ጠመዘዙት። ሥልጣን የገንዘብ ምንጭ ነውዕ አሉ አቶ መለስ፣ ገንዘብ የኃጢዓት ሁሉ ምንጭ ነው የሚለውን ዘንግተው። ይህን መጻፌ የታሪኩን ሂደት ለማብራራት እንጂ ሙት ወቃሽ ሆኜ አይደለም።
አቶ መለስ ኢትዮጵያን የሚያህል ትልቅ አገር ማስተዳደር እንደማይችሉ ገና ከጠዋቱ ያውቁ ነበር። አቶ መለስ እነ አጼ አምደጽዮንን፣ አጼ ገላውዲዎስን፣ አጼ ሚኒልክን የሚተካ የአመራር ችሎታ ይቅርና በቅርብ በታሪክ ከሚታወቁት ጀግናው ራስ አሉላ፣ ራስ ጎበና ወይም ራስ መስፍን ጋር እንኳን የሚተካከል ያንዲት ሳንቲም ክፋይ ጀግንነትም ይሁን ማስተዋል እንደሌላቸው ስብዕናቸው ጠንቅቆ ያውቃል። አቶ መለስ ከሻዕቢያ ጋር የተስማሙት ትግራይን ታላቋ ትግራይዕ ብለው ከልለው ወይም ገንጥለው ወደብ ለኢትዮጵያ እያከራዩ ገንዘብ እንደ ውሃ ቦና የሚሰበስቡ መስሏቸው ነበር። ይህን ምስጢር የኤርትራም የትግራይም ሕዝብ አያውቅም። አቶ መለስ ስለ ገንዘብ ሲያስቡ ገንዘቡን ለልጆቻቸው እየሰጡ በውጭ ሃገር እያንደላቀቁ ሊያኖሯቸውም ጭምር አስበው ነበር። ይህ ሃሳብ በማኦ ሴቱንግ መጽሃፍ ላይ እንዴት እንደተጻፈ አላውቅም። አቶ መለስ ግን ትርጉሙ ገብቷቸዋል። አጠገባቸው ካሉት ውስጥ ትልቁ አቦይ ካልሆኑ በቀር ተራ ተጋዳላዮቹ ሊገለጽላቸው አይችልም። የአቶ መለስን ራዕይ የሚያውቁት ባለቤታቸው ብቻ ናቸው። እሳቸውም ቢሆን በድንግዝግዙ ነው።
አቶ መለስ ስለገንዘብና ስደት ሲያውጠነጥኑ የመንገዳቸውን መጀመርያ ያደረጉት መውጫ፣ መላወሻ፣ መፈርጠጭያ፣ መጋለብያ መሬቶችን ማፈላለግ ነበር። ይህን ጊዜ የቅዱሳን ምድሯ ዋልድባ፣ የሰሊጥ አምራችዋ ሁመራ፣ የጀግኖቹ ምድር ወልቃይጥ፣ ጠለምትና ጠገዴ ፈረደባቸው። አቶ መለስ ችግር ከመጣ ወደ ሱዳን ለመጠጋት እነዚህን መሬቶች ከትግራይ ጋር መደባለቅ ሊኖርባቸው ነው። እስከዛው ድረስ ግን ለሟን መሬት ይበዘብዛሉ። ፍርጃ ማለት ይህ ነው። አቶ መለስ የማኦ ሴቱንግን መጽሃፍ ብቻ ሳይሆን የኢጣልያ የቅኝ ግዛት ካርታንም ከየትም አፈላልገው ሲያጠኑት፣ ሲያስተውሉት ይኖሩ ነበር። ኢጣልያ በዘር ከፋፍላ ለመግዛት እንዲያመቻት አልያም ከጦር ስትራቴጂካዊነት አኳያ ወድያና ወዲህ አደበላልቃ፣ ከልሳ አከላልሳ የፈጠረችውን የዘር ክልሎች አቶ መለስ ያገናዝቧቸው ነበር። እነዚህ ናቸው የአቶ መለስ ፍልስፍና ፈር ቀዳጆች፣ የቻይናው ማኦ ሴቱንግ ሥልጣን (ገንዘብ) ከጠመንጃ አፈሙዝ ይወለዳል ና የኢጣልያ የዘር ክልል ካርታ። እነዚህ ናቸው አቶ መለስን በደጋፊዎቻቸው ዘንድ እንደ ናፖሊዎን ስትራቴጂካዊ፣ እንደ አዳም ስሚዝ ልማታዊ፣ እንደ ሆ ቺሚንህ ነጻ አውጭ፣ እንደ ኢንቫዮርሜንቱ ሳይንቲስቶቹ ሊቃዊንት ያስባላቸው። በእርግጥ አቶ መለስ እግዚአብሄር የሰጣቸውን አዕምሮ በመልካም ቢጠቀሙበት ኖሮ ለሃገራቸው ይጠቅሙ ነበር። ይህ አለመሆኑ በጣም ያሳዝናል።
ከወልቃይት ብሎግ ባገኘሁት ማስረጃ መሠረት ከአንገረብ ወንዝ በስተ ሰሜን የሚገኙት ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ዋልድባ፣ ጠለምት፣ ሰሜን፣ ዋገራ ከአገው ፈላሻ የተወረሰ የራሳቸው ባህል፣ ኃይማኖትና ቋንቋ እንዳላቸው ነው። እነዚህ ሃገሮች በተከዜ በኩል ከትግራይ ጋር ስለሚዋሰኑ የንግድ ልውውጥ ያደርጉም ነበር። የወቅቱ የአክሱም ትግራይ የበላይነት መንፈስ የግዕዝ ትግሬኛ ቋንቋ በተለይ በወልቃይት ውስጥ እንዲሰርጽ ምክንያት ሆኗል። ጠለምትም ከትግራይ በሚሾመው በሹም ጠለምት በመተዳደርዋ እስከ አስራ ስድስተኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ድረስ ለትግራይ አስተዳደር ትገብር ነበር። የኦሮሞ ሕዝብ ከደቡብ ወደ ሰሜን መስፋፋት ሲጀምሩ የአማራ፣ አንጎትና ሸዋ ንጉሳዊ አስተዳደር ተፋለሰ። ሕዝቡም ከአባይ ማዶ ሰሜናዊ ግዛት ትግራይ አጠገብ መስፈር ጀመረ። ነገሥታቱ ኃይላቸው በመመናመኑ ምክንያት ከጣና ሃይቅ ሰሜን በደንብያና ወልቃይት ሠፋሪ የነበረውን አገውና ፈላሻን በመውረር ክርስትያን ኃይማኖትን በግድ እንዲቀበል አደረጉት። ይህ አዲሱ አካባቢ በአማራ ንጉሳዊ አስተዳደር ስር ተማከለ። ቋንቋቸውም ልሳነ ንጉሥ የሆነው አማርኛ ሆነ። ከዚህ ቀደም የነበረው ምዕራብ ተከዜን አስታኮ የነበረው የትግራይ ገዥዎች ተፅዕኖም ፈጽሞ ተቋረጠ። ይህ ሁኔታ ከዘመነ መሳፍንት አንስቶ በአጼ ቴዎድሮስ፣ በትግራዩ ንጉሥ ዮሃንስ፣ በአጼ ሚኒልክ፣ በኢያሱና ዘውዲቱ፣ በቀዳማው ኃይለ ሥላሴና ደርግ ድረስ አንዳች ለውጥ አልተደረገበትም። ጎንደር የኢትዮጵያ ማዕከላዊነቷ ተቋርጦ ዋና ከተማው አዲስ አበባ ሲዞርም እንኳን ይህ ይዞታ ለውጥ አልተደረገበትም ነበር።
ፋሺስት ኢጣልያ ኢትዮጵያን ዳግመኛ ስትወር ከአንገረብ ወንዝ ሰሜን ያሉትን የጎንደር ክፍለ ግዛት ከኤርትራ ጋር ደባለቀችው። ኢጣልያ ይህን ያደረገችው ወታደራዊ የገዥ መሬት ከመያዝ አኳያና በአካባቢው ያለውን የአርበኞች ትግል ለመቆጣጠር ነበር። አካባቢው በተለይም ሰሜን፣ ጠለምት፣ ወልቃይትና ጠገዴ ከጥንት ጀምሮ የአመጽና የሽፍቶች መሰማርያ ነበር ይባላል። ከአንገረብ ወንዝ ደቡብ የሚገኘውም ታሪካዊው አካባቢ እስከ ሱዳን ጠረፍ ኦም ሃጀር ድረስ የሚያካልለው አርማጭሆ ለኢጣልያ አስጊ አካባቢ ነበር። ፊታውራሪ ውብነህ ወይም አሞራው ውብነህና ቢትወደድ አዳነ መኮንን በዚሁ አካባቢ ሸፍተው ኢጣልያን መውጫ መግቢያ ያሳጡ ጀግኖች ነበሩ። ቢትወደድ አዳነ የኢትዮጵያ ዲሞክራቲክ ሕብረት (ኢዲዩ) መሪ ሆነው ደርግን በመፋለም ላይ እንዳሉ ኢሕአፓ በሰማንያ አራት አመታቸው ሱዳን ድንበር አካባቢ በግፍ ገደለቻቸው።
አቶ መለስ ይህን የኢጣልያ ዘረኛ ካርታ ሙሉ በሙሉ ሥራ ላይ በማዋል ግማሹን በጌምድር ከምዕራብ ትግራይ ጋር አደባለቁ። ለሞቹ የአንገረብ ወንዝ አካባቢዎች ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ዋልድባና ጠለምት ከትግራይ ጎን የሚገኙ አካባቢዎች በመሆናቸው ከእሾህ የተጠጉ አጋሞች ሆኑ። የትግራይ ትግርኝ የአቶ መለስ ፕሮጀክት ሕዝቡን በማይፈልገው አሳዛኝ ተፅዕኖ ሥር አምበረከከው። ባጠቃላይ አቶ መለስ በምስራቅ ከቀይ ባህር ጋር ለመገናኘት ጢዮን ወይም መርስ ፋትማን ለማካለል እያሰቡ በሌላ በኩል ደግሞ ከሱዳን ጋር ለመዋሰን በጋሽና ሰቲት ወንዝ መሃከል ያሉትን አካባቢዎች በመንጠቅ እንዲሁም እስከ ምዕራብ ወሎ ዋግ ክልልን በማስገባት ገንዘብ የማሰባሰብ ዓላማቸውን ያሳኩ ዘንድ የዕብሪት ራዕያቸውን ከፍ አደረጉ። የሠመረላቸው ሰምሮ የተቀረውን የቤት ሥራ ለተባባሪዎቻቸው አስረክበው እስከ ወድያኛው አሸለቡ።
የአቶ መለስና ተባባሪዎቻቸው የትግራይ ትግርኝ ፕሮጀክት በምን ምክንያት ጋብ አለ። አንደኛ አሜሪካ ሶሻሊስታዊ አስተሳሰባቸውን ካቆሙ ሥልጣን ላይ እንደሚያወጣቸው ለአቶ መልሰ በግልጽ ነገረቻቸው። እሺ በማለታቸው አዲስ አበባ ሚኒልክ ቤተመንግሥት በሰላም ገቡ። ሁለተኛ ከአቶ ኢሳያስ ጋር የተማማሉበት ትግራይን ገንጥሎ ወደብ ሸጦ ገንዘብ የመሰብሰብ እቅዳቸው በሌላ አዲስ እድል ተተካ። መላ ኢትዮጵያን ከያዙ በርካታ እንደውም ካሰቡት በላይ ገንዘብ ስለሚያገኙ ወደብ ሽያጩን ናቁት። ይባስ ብለው ከእቶ ኢሳያስ ጋር በገንዘብ ምክንያት ሲጣሉ ወደ አላስፈላጊ ጦርነት ገብተው ብዙ ሰዎች ተሰዉ። አሰብ የግመል መፈንጫ ነው የምትሆነውዕ ብለው ወደ ማህል ኢትዮጵያ ዘልቀው ገቡ። ያደቆሰ ሰይጣንዕ እንደሚባለው ገንዘብ እያሸተቱ ይበልጥ ወደ መሃል ተሳቡ። ኦርቶዶክስንና አማራን አከርካሪውን ሰብረነዋልዕ አሉ አቦይ ስብሃት የዋልድባንም የመሬት ሸንኮራአገዳ ሊተክሉበት እያሰቡ። ዋልድባ አለቀሰች፣ አነባች ሁለቱን እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ዘረጋች። አቶ መለስና ባለቤታቸው፣ አቶ መለስና ተባባሪዎቻቸው፣ አቶ መለስና ዘመዶቻቸው በኢንቬስትሜንት ስም፣ በልማት ዘፈን ለሟን ኢትዮጵያ ከላይ አርማጭሆ እስከታች ሞያሌ መጠመጧት። ልጆቻቸውን ገንዘብ እየሰጡ በውጭ ያዝናኗቸው ጀመር። የኢትዮጵያ ወጣቶችም ሃገራቸውን እየለቀቁ ሲሰደዱ ልጃቸው መንገድ ዳር እየተጸዳዳች ፎቶ ትነሳ ጀመር። ይህ በእንዲህ እንዳለ አቶ መለስና ጳጳሱ ድንገት ሞቱ። የባለቤታቸው፣ ተባባሪዎቻቸውና ኢንቨስተሮቻቸው ገንዘብ የማሰባሰብ ዘዴና ትልም በአጭረ ተቀጨ። ሌላ ስትራቴጂ የሚያመነጭ ጠፋ። የተማሩ ናቸው ተብለው የተቀመጡትም አቶ ኃይለማርያም ትምህርቱ ተሰወረባቸው። በድንገት ኦሮምያ ላይ አመጽ ፈነዳ። የመለስ ፋውንዴሽን፣ የሼኩ ንብረቶች፣ የውጭ ኢንቬስተሮች ተቋም፣ የልማታዊው ዲያስፖራው ሱቆች በእሳት ጋዩ፣ በድንጋይ ተወገሩ። የአቶ መለስ የብዝበዛ ፍልስፍና በአጭር ሊቀጭ ሆነ። የኦሮምያ ወጣቶች ሆ ብለው ተነሱ። ወተቷን ጠጥተው፣ እሸቷን በልተው ያደጉትን ልማታዊ ኦሮሞዎችንም አስጠነቀቁ። እነዚህ ሁል ያመጹት ወጣቶች የልማቱን ዘፈንዕ እየሰሙ ያደጉ ወጣቶች ናቸው።
ለም በመሆንዋ ከትግራይ ጋር ሳትወድ የተደባለቀችው መሬት ድምጿን ከፍ አድርጋ ጮኸች። ጊዜ ጥሏት ማንነቷን የተነጠቀችው ያች የቅዱሳን መሬት አመጸች። ከወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት፣ የአማራውን ሕዝብ እያፈናቀሉ ከትግራይ ሰዎች እያሰፈሩበት በውሳኔ ሕዝብ (ረፈርንዱም) ስልት አካባቢን ከትግራይ ጋር ለመደባለቅ የወጠኑት ስልትም ተቀባይነት የለውም። ይህ ቢደረግ ታሪክ ትፋረዳለች፣ ዋልድባ ታለቅሳለች፣ ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሄር ትዘረጋለች። እርሱ አምላክ ከላይ ከከፍታው መብረቅ ያወርዳል። ያች መውጫ፣ መላወሻ፣ መፈርጠጭያ፣ መጋለብያ ተብላ በግፍ የተወሰደች የወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምት ለም መሬት፣ ለቅዱሳኑ ኪዳናት ባለአደራ የሆነችው ዋልድባም ጭምር መወለጃ መሆኗ ቀርቷል። እናንተ እብሪተኞች ያጽመ ርስት ይዞታዎቼን ልቀቁልኝ አለች።
ከላይ እንዳነሳሁት ጃንሆይም፣ ኮሎኔል መንግሥቱም አቶ መለስም ለልጆቻቸው ያሰቡ አይመስለኝም። የጃንሆይ ልጆች፣ የልጅ ልጆች ስደተኞች ሆኑ። የኮሎኔል መንግስቱም ልጆች እሳቸውም ስደተኞች ሆኑ። የአቶ መልሰ ልጆች ግን ስደተኛ እንኳን ሆነው መኖር የሚችሉ አይመስለኝም። አባታቸው ሥጋዊ ኑሯቸው የሲዖል ኑሮ እንደሆነባቸው አሸለቡ። ልጆቻቸውም ገንዘብ ታቅፈው ወደ ውጭ ሊኖሩ የሚችሉበት የዓለም ክፍል የለም። የአለም አቀፍ ህግ ተሻሽሏል። ባለቤታቸው፣ ሌሎቹም የራዕዩ ወራሾች በሁመራ አግርገው ወደ ሱዳን እንዳይፈረጥጡ ወደ ማህል ተስበው እግሮቻቸው በዝርፍያ ከተሠሩት ሕንፃዎች መሠረት ጋር አብሮ ወደ መሬት ተቀበረ። እጆቻቸው ከንግድ ቤቶቻቸው ግድግዳና ከኤፈርቱ የሙስና ኃብት ጋር ተጣበቁ። እንዴት ይውጡ፣ ወዴት ይሰደዱ። ቢሰደዱም ያሰደዷቸው ወጣቶች በየትኛውም የዓለም ክፍል ይጋፈጧቸዋል። አሁንም መከራ እያዩ ነው።
ከእሾህ የተጠጉት ወልቃይት፣ ጠገዴ፣ ጠለምትና ዋልድባ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ አለቀሱ። ኦሮምያም አነባች፣ ተጋጠች፣ ከብቶቿ ታለቡ፣ ወርቋ ተዘረፈ። መላ ኢትዮጵያ ቆሰለች። ለአቶ መለስና ተባባሪዎቻቸው ሥልጣኑን ለሕዝቡ በሠላም እንዲያስረክቡ አሁንም ዕድሉን አልተነፈጉም። ይህ ካልሆነ ውሎ አድሮ ምን እንደሚፈጠር ሳይገነዘቡት አይቀሩም። የዝርፍያ፣ የቀማኝነትና የቁማር ፖለቲካ አሜሪካ የቱንም ያህል ቢረዳው መጨረሻው አያምርም።
እባክህ እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ከስቃይ አውጣት። መች ይሆን ሕዝብህ እፎይ የሚለው፧

Wednesday, August 17, 2016

ወያኔዎች ሆይ

ወያኔዎች ሆይ ልብ ልትገዙ ይገባል፡፡ የህዝብን ቁጣ ጥቂቶች የፈጠሩት ሁከት ነው እያሉ በሕዝብ ላይ መሳለቃችሁን አቁሙና ከማናቸውም የኃይል እርምጃ በመታቀብ ሕዝብ የሚላችሁን ብታደምጡ ይበጃል፡፡ ህዝቡ በቃችሁኝ ብሉአል ያላቹ ጊዜ በጣም አጭር ነዉ፡፡ ከረፈደ ይሄንን እድል አታገኙም፡፡

Monday, August 15, 2016

ወያኔ 
እነሆ እኛ ኢትዮጵያዉያን ህብረት፣ መደጋገፍ፣ ስምምነትና አርቆ አሳቢነት 
የሚጠይቅበት ወሳኝ ወቅት ላይ ደርሰናል። ያለፉት ዓመታት የወያኔውን ጥቁር ሥርዓት ምንነት አሳይቶናል። ይህንን ብቻ አይደለም፤ በአምባገነን ሥርዓትና ለቅኝ ገዥዎች በባንዳነት በሚያድር ሥርዓት መካከል ያለውን ልዩነትም በሚገባ አሳውቆናል። የንጉሡ ዘመን ኋላ ቀር ነበር። የደርግ ዘመን አምባገነን ነበር። በሁለቱም ሥርዓት ወቅት ግን ሃገር ነበረች። ኢትዮጵያ እስከ ባህረ በሯ ሉዓላዊ እስከ ሕዝቦቿ ክቡር ነበረች። ዛሬ ለየት ያለ ነው። ወያኔ ዘረኛ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሙስናዊ አምባገነን ሥራዓት ቋሚ ተጠሪ ስብስብ ተቋም ብቻ አይደለም። ወያኔ "የአናቁረህ ግዛ" ግፍ አራማጅ ብቸኛ የቀማኞች ድርጅት ብቻ አይደለም። ወያኔ ቅድስት ሃገር ኢትዮጵያን ለውጭ ባለሃብቶች የሸበሸበ የኃጢአተኞችና "የአስረሽ ምቺ" ዳንኪረኞች፣ መዝባሪዎች ስብስብ ብቻ አይደለም። ወያኔ የሁሉም የኃጢዓት ሥርዓቶች ድምር ነው። ወያኔ ድንገት ከተሰባሰበበት ደደቢት ሸለቆ ተንከባሉ ሠይጣን ዋሻ ውስጥ ለአመታት ከርሞ ዲያቢሎስ ሳያኝክ የተፋው የርኩስ ሥርዓት ቁንጮ ነው። እድሏ ሆኖ ቅድስት ኢትዮጵያ የዚህ ሥርዓት ተሸካሚ ሆናለች። እንዲያ እንዳልተከበረች፣ እንዲያ እንዳልተፈራች ሃገራችን ኢትዮጵያ ለቅኝ ገዥዎች ቅርጫ ቀረበች። ሥርዓቱ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ ኢትዮጵያን በቁሟ የገነዘ፣ ሕዝቧን ያስጨነቀ መሪር ሥርዓት ነው። ኢትዮጵያ ሃገራችንን ከዚህ ሥርዓት የሚገላግላት ቆራጥነትና በህብረት መነሳት ብቻ ነው። ህዝብን በመርዘኛ ራዕይ ሰልቦ፣ ወጣቱን በሥራ አጥነት አጠውልጎ ለስደትና ሴተኛ አዳሪነት እየዳረገ፣ ነዋሪውን በልማት ስምና በከተማ ማስፋፋት እያፈናቀለ ሕዝብን በቅኝ ገዥዎች ቋንቋና በምጣኔ ኃብት እድገት እያደናገረ የሃገሪቱን ሃብት መዝብሮ ወደ ውጭ በማሸሽና በከፍተኛ ዕዳ ውስጥ በመዝፈቅ በጥቂቶች ስም ሃብት እያከማቸ እስከ ዓለም ፍጻሜ ሊገዛ የሚቃጣ ዘመነኛ የግፍ ሥርዓት አራማጅ ወያኔ ብቻ ነው።

Thursday, August 11, 2016

ነሃሴ ፭ ( አምስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚደርሱን መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ገዢው ፓርቲ በአማራ እና በኦሮምያ ክልሎች የተነሳውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለማስቆም የጸጥታ ሃይሉን በብዛት በማሰማራት ውጥረቱን አባብሶታል። የፌታችን ቅዳሜ እና እሁድ ተቃውሞ ይካሄድባቸዋል በሚባሉት በርካታ የ አማራ ክልል ወረዳዎች ብዛት ያላቸው የመከላከያ ሰራዊት አባላት እና የፌደራል ፖሊሶች እየገቡ ሲሆን፣ ተቃውሞውን ሊያስተባብሩ ይችላሉ የተባሉት ደግሞ እየታፈሱ ወደ እስር ቤት እየተጋዙ ነው። በተለይ በደብረማርቆስ ውጥረቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መደርሱን የከተማዋ ነዋሪዎች ለኢሳት ተናግረዋል። በክልሉ ዋና ከተማ ባህርዳርም እንዲሁ የፊታችን እሁድ የተቃውሞ ሰልፍ በድጋሜ ሊጀመር ይችላል ተብሎ እየተነገረ መሆኑን ተከትሎ ወታደሮች ጥበቃቸውን አጠናክረዋል። በዛሬው እለት አንዳንድ ንግድ ድርጅቶችና የትራንሰፖርት መኪኖች እንቅስቃሴ ቢጀምሩም አብዛኛው ወጣት ከወታደሮች እይታ ውስጥ ላለመግባት ጊዜውን በቤቱ ማሳለፍን መርጧል። በአንድ ላይ ሰብሰብ ብለው መንገድ ላይ የተገኙ ወጣቶች እየተያዙ በመታሰር ላይ ናቸው። የክልሉ ጤና ቢሮ ሰራተኞች የታሰሩት ካልተፈቱ ስራ አንጀምርም ማለታቸውን ነዋሪዎች ገልጸዋል። የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ክልሉን በብቃት አልመሩም በሚል ወሳኝ የሚባሉትን ጉዳዮች የፌደራል ባለስልጣናት መስጠት የጀመሩ ሲሆን፣ አቶ ገዱን በሂደት ከስራ እንቅስቃሴ ውጭ ለማድረግ እንቅስቃሴዎች መጀመራቸውን ምንጮች ገልጸዋል። አብዛኛውን የክልሉን እንቅስቃሴ በፌደራል ደረጃ በሚሰሩ የህወሃት ታማኞች ለመምራት የሚያስችል አሰራሮች መተግበር ጀምረዋል። በወልድያ ዛሬ የባጃጅ አሽከርካሪዎችንና ባለንብረቶችን ለመሰብሰብ የተደረገው ሙከራ እንዲበተን ተደርጓል። በሰሜን ወሎ ዋና ከተማ ወልድያ ፣ በባህል አዳራሽ የተጀመረው ስብሰባ በክልሉ የትራንስፖርት ሃላፊ የተመራ ሲሆን ፣ ከ200 ያላነሱ ሹፌሮችና ባለሃብቶች ብቻ በስብሰባው ላይ ተገኝተዋል። ስብሰባው በጭቅጭቅ መሞላቱን ተከትሎ ተሰብሳቢዎች አዳራሹን ለቀው የወጡ ሲሆን ፣ እንደገና በልመና 30 የሚሆኑ ሰዎች ስብሰባውን ተካፍለዋል። በመጨረሻም የጸጥታ ሃላፊው አቶ ሙልቀን ማርዬ በእሁድ ስልፍ ላይ እንዳትወጡ በማለት መስጠንቀቂያ ሰጥተዋል። ተመሳሳይ ስብሰባዎች በከተማዋ የተለያዩ ቀበሌዎች ተካሂዷል። በላሊበላ ከተማም እንዲሁ ካድሬዎች በየፅ/ቤቱ፣በየቀበሌውና በየትምህርት ቤቱ ህዝቡን በመሰብሰብ በእሁዱ ሰላማዊ ሰለፍ ብትሳተፉ ወዮላችሁ እያሉ በማስጠንቀቅ ላይ ናቸው፡፡ በርካታ የገጠር ሚኒሻዎች እና የአካባቢ ፖሊሶች ከተማይቱን የወረሩ ሲሆን አቶ ግርማ የተባለ በልስ ስፌት የሚተዳደር ሰው ትቀሰቅሳለህ በሚል ተይዞ ታስሯል። በደብረብርሃን ከተማም ተመሳሳይ ስብሰባ ተካሂዶ ተበትኗል። በከተማዋ የጸጥታ ሃይሎች እየዞሩ ህዝቡን በማስፈራት ላይ ናቸው። በአዊ ዞን ቻግኒ ከተማ የሚገኙ ነዋሪዎች ትናንት የተቃውሞ ሰልፍ ለማዘጋጀት ሲሞክሩ በፖሊሶች የተዋከቡ ሲሆን፣ የተቃውሞውን ሰልፍ በሳምንቱ መጨረሻ ለማካሄድ እንዳቀዱ ተናግረዋል። ባለፈው ቅዳሜ ከአዲስ አበባ የታፈሱ 1 ሺ የሚሆኑ ወጣቶች በአዋሽ አርባ መታሰራቸውን ለማውቅ ተችሎአል። የደህንነት ሃይሎች የታሰሩትን ለመጠየቅ የሚሄዱ ሰዎችን ገንዘብ ስጡንና እንፈታቸዋለን ማለት መጀመራቸውን ለጥየቃ የሄዱ ቤተሰቦች ተናግረዋል። ድርጊቱ ያስገረማቸው የእስረኞች ቤተሰቦች ፣ “ደህንነቶች የሚጠይቁት ገንዘብ ማንኛውም ደሃ ህዝብ ሊከፍለው የማይችለው ነው” ካሉ በሁዋላ ፣ ደህንነቶች ሁኔታው አስግቷቸው ገንዘብ መሰብሰብ የጀመሩ ይመስለናል ሲሉ ትዝብታቸውን አክለዋል።

Monday, August 8, 2016

ሰበር ዜና በመቶዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች ሰሮቃን ለቀው በመውጣት በየጫካው መሽገዋል። ሴቶችና ህጻናት ሰሮቃ ከተማ ለቀው ወጥተዋል። ትናንት በሚሊሺያዎችና በወታደሮች መካከል የነበረው ፍጥጫ በሽማግሌዎች እንዲበርድ ቢደረገም፣ ገዢው ፓርቲ ራሱ ያስታጠቃቸው አርሶአደር ታጣቂዎች ከእንግዲህ በህወሃት አንገዛም በማለት ጫካ በመግባታቸው በማንኛውም ጊዜ ጦርነት ሊነሳ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። 3 ታንኮች እና በ6 ኦራል መኪኖች የተጫኑ ወታደሮችም ሰሮቃን ለቀው ወደ ማክሰኚት አቅጣጫ በማምራት ላይ ይገኛሉ። ከዳንሻ የመጣ ጦር ሰሮቃ የነበረውን ጦር ተክቶ ከተማዋን ተቆጣጥሯል። ከጎንደርና ሁመራ የተነሳ ጦር ወደ አርማጭሆ እየሄደ ነው። በትክል ድንጋይ አካባቢ 7 ወታደሮች ዛሬ ጠዋት ተገድለዋል። በሰሜን ጎንደር ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።

Tuesday, August 2, 2016

ሐምሌ ፳፮ ( ሀያ ስድስት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና

ሐምሌ ፳፮ ( ሀያ ስድስት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የተጻፈውና በቅጅ ለኢሳት የተላከው ደብዳቤ ፣ “ በእብሪተኛ ገዢዎች እየተፈጸመ ያለው ግፍ በሃገርና በህዝብ ላይ የደገሰውን የሞት ድግስ ከማድረሱ በፊት የሚመለከታቸው ወገኖች ሁሉ አፋጣኝ መልስ እንዲሰጡ እንጠይቃለን ብሎአል። ደብዳቤው በጎንደር ባለፈው እሁድ ተካሂዶ በነበረው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የቀረቡት ጥያቄዎች በአፋጣኝ መልስ እንዲያገኙ ይጠይቃል። በግፍ ታፍነው የተወሰዱት የወልቃይት የማንነት ጥያቄ አቅራቢ ህዝብ ወኪሎች የሆኑት አቶ አታላይ ዛፌ፣ አቶ ጌታቸው አደመ፣ አቶ አለነ ሻማ፣ አቶ መብራህቱ ጌታሁንና ሌሎችም የተጣለባቸውን የህዝብ አደራ አቤቱታ በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለመንግስት ከማቅረባቸው ውች ሌላ ምንም ከህዝብ እይታ የተሰወረ የሰሩት ወንጀል ሳይኖር ሆን ተብሎ የጥያቄውን መስመር ለማስቀየር የሃሰት ውንጀላ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ይጠይቃል። የወልቃይት አማራ ማንነት ጥያቄ በአስቸኳይ እንዲፈታ፣ ከ2007 ዓም ጀምሮ በሰሜን ጎንደር በአንድነት የሚኖሩ ቤተሰቦችን አማራ ቅማንት የሚል ከፋፋይ ሴራ በመፍጠር በተለያዩ ጊዜ በሽፋን ጭልጋ ትክል ድንጋይ ሮቢት ማውራና ሌሎች ቦታዎች ለሞቱትና ያለ አገባብ ለታሰሩት ወንድሞችንና እህቶች የሃሳቡ ጠንሳሾች፣ አስፈጻሚና ፈጻሚ ተጠያቂዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ ሃምሌ 5 2008 ዓም በጎንደር ደህንነትና ጸረ ሽብር ግብረ ሃይል በመግለጫ ያስተላለፉት መልእክት ፍጹም የተሳሳተና ውሸት በመሆኑ ማስተባበያ በመስጠት የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ እንዲጠይቁም ደብዳቤው ይጠይቃል። “ከዚህ በሁዋላ በኦሮምያ ጋምቤላ ቤንሻንጉልና ሌሎችም የኢትዮጵያ መሬቶች በኢትዮጵያውያን የሚቀርቡ ሰላማዊ ጥያቄዎችን በተጠየቁበት በሰላማዊ መልስ ከመስጠት ውጭ ሻዕቢያ ቅጠረኛ ሽብርተኛ የሚል የሃሰት ስም በመለጠፍ እራሱ በሚከፍላቸው ሰራዊቶች፣ በእራሱ ገንዘብ በተገዛ መሳሪያ በማፈን በመግደል ሰላማዊ ጥያቄዎችን ለመድፈቅ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ እንዲቆምና እንዳይሞከር በጥብቅ እናሳስባላን” የሚለው ደብዳቤው ፣ ለእነዚህ ጥያቄዎች አፋጣኝ መልስ እንዲሰጠም ጠይቋል። የሳንጃ ነዋሪዎች እና ታጣቂዎች ጎንደር ከተማ ገብተው የተቃውሞ ድምጻቸውን ካሰሙ በሁዋላ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ምሽት ላይ ህዝቡ በጀግና አቀባባል ተቀብሎአቸዋል። በጎንደር እና በእስቴ ወረዳ በመካነየሱስ ከተማ የተካሄዱትን ተቃውሞዎች ተከትሎ ተመሳሳይ ተቃውሞች በመጪው እሁድ በባህርዳር ፣ በደብረታቦር እንዲሁም በመካነሰላም በድጋሜ ለማካሄድ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው። ሰልፎቹ በጎንደር የሚካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመደገፍ የተጠራ ነው።