ሰበር ዜና በመቶዎች የሚቆጠሩ ታጣቂዎች ሰሮቃን ለቀው በመውጣት በየጫካው መሽገዋል። ሴቶችና ህጻናት ሰሮቃ ከተማ ለቀው ወጥተዋል። ትናንት በሚሊሺያዎችና በወታደሮች መካከል የነበረው ፍጥጫ በሽማግሌዎች እንዲበርድ ቢደረገም፣ ገዢው ፓርቲ ራሱ ያስታጠቃቸው አርሶአደር ታጣቂዎች ከእንግዲህ በህወሃት አንገዛም በማለት ጫካ በመግባታቸው በማንኛውም ጊዜ ጦርነት ሊነሳ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል። 3 ታንኮች እና በ6 ኦራል መኪኖች የተጫኑ ወታደሮችም ሰሮቃን ለቀው ወደ ማክሰኚት አቅጣጫ በማምራት ላይ ይገኛሉ። ከዳንሻ የመጣ ጦር ሰሮቃ የነበረውን ጦር ተክቶ ከተማዋን ተቆጣጥሯል። ከጎንደርና ሁመራ የተነሳ ጦር ወደ አርማጭሆ እየሄደ ነው። በትክል ድንጋይ አካባቢ 7 ወታደሮች ዛሬ ጠዋት ተገድለዋል። በሰሜን ጎንደር ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሷል።
Monday, August 8, 2016
Tuesday, August 2, 2016
ሐምሌ ፳፮ ( ሀያ ስድስት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና
ሐምሌ ፳፮ ( ሀያ ስድስት ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- ለተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የተጻፈውና በቅጅ ለኢሳት የተላከው ደብዳቤ ፣ “ በእብሪተኛ ገዢዎች እየተፈጸመ ያለው ግፍ በሃገርና በህዝብ ላይ የደገሰውን የሞት ድግስ ከማድረሱ በፊት የሚመለከታቸው ወገኖች ሁሉ አፋጣኝ መልስ እንዲሰጡ እንጠይቃለን ብሎአል። ደብዳቤው በጎንደር ባለፈው እሁድ ተካሂዶ በነበረው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ የቀረቡት ጥያቄዎች በአፋጣኝ መልስ እንዲያገኙ ይጠይቃል። በግፍ ታፍነው የተወሰዱት የወልቃይት የማንነት ጥያቄ አቅራቢ ህዝብ ወኪሎች የሆኑት አቶ አታላይ ዛፌ፣ አቶ ጌታቸው አደመ፣ አቶ አለነ ሻማ፣ አቶ መብራህቱ ጌታሁንና ሌሎችም የተጣለባቸውን የህዝብ አደራ አቤቱታ በሰላማዊና ህጋዊ መንገድ ለመንግስት ከማቅረባቸው ውች ሌላ ምንም ከህዝብ እይታ የተሰወረ የሰሩት ወንጀል ሳይኖር ሆን ተብሎ የጥያቄውን መስመር ለማስቀየር የሃሰት ውንጀላ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ይጠይቃል። የወልቃይት አማራ ማንነት ጥያቄ በአስቸኳይ እንዲፈታ፣ ከ2007 ዓም ጀምሮ በሰሜን ጎንደር በአንድነት የሚኖሩ ቤተሰቦችን አማራ ቅማንት የሚል ከፋፋይ ሴራ በመፍጠር በተለያዩ ጊዜ በሽፋን ጭልጋ ትክል ድንጋይ ሮቢት ማውራና ሌሎች ቦታዎች ለሞቱትና ያለ አገባብ ለታሰሩት ወንድሞችንና እህቶች የሃሳቡ ጠንሳሾች፣ አስፈጻሚና ፈጻሚ ተጠያቂዎች ለፍርድ እንዲቀርቡ፣ ሃምሌ 5 2008 ዓም በጎንደር ደህንነትና ጸረ ሽብር ግብረ ሃይል በመግለጫ ያስተላለፉት መልእክት ፍጹም የተሳሳተና ውሸት በመሆኑ ማስተባበያ በመስጠት የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ እንዲጠይቁም ደብዳቤው ይጠይቃል። “ከዚህ በሁዋላ በኦሮምያ ጋምቤላ ቤንሻንጉልና ሌሎችም የኢትዮጵያ መሬቶች በኢትዮጵያውያን የሚቀርቡ ሰላማዊ ጥያቄዎችን በተጠየቁበት በሰላማዊ መልስ ከመስጠት ውጭ ሻዕቢያ ቅጠረኛ ሽብርተኛ የሚል የሃሰት ስም በመለጠፍ እራሱ በሚከፍላቸው ሰራዊቶች፣ በእራሱ ገንዘብ በተገዛ መሳሪያ በማፈን በመግደል ሰላማዊ ጥያቄዎችን ለመድፈቅ እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ እንዲቆምና እንዳይሞከር በጥብቅ እናሳስባላን” የሚለው ደብዳቤው ፣ ለእነዚህ ጥያቄዎች አፋጣኝ መልስ እንዲሰጠም ጠይቋል። የሳንጃ ነዋሪዎች እና ታጣቂዎች ጎንደር ከተማ ገብተው የተቃውሞ ድምጻቸውን ካሰሙ በሁዋላ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ምሽት ላይ ህዝቡ በጀግና አቀባባል ተቀብሎአቸዋል። በጎንደር እና በእስቴ ወረዳ በመካነየሱስ ከተማ የተካሄዱትን ተቃውሞዎች ተከትሎ ተመሳሳይ ተቃውሞች በመጪው እሁድ በባህርዳር ፣ በደብረታቦር እንዲሁም በመካነሰላም በድጋሜ ለማካሄድ ዝግጅቶች እየተካሄዱ ነው። ሰልፎቹ በጎንደር የሚካሄደውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመደገፍ የተጠራ ነው።
Friday, July 8, 2016
ኤስፍና ESFNA እና AESA One ታሪካዊ ግብግብ
ኤስፍና ESFNA እና AESA One ታሪካዊ ግብግብ
ከ ሚኪያስ ግዛው
በሁለቱም ሜዳዎች ላይ ባንዲራዎች ይውለበለባሉ። በሁለቱም ሜዳዎች ላይ ኳሶች ይነጥራሉ። በሁለቱም ሜዳዎች ላይ ድምጻውያን ይዘፍናሉ። በሁለቱም ሜዳዎች ላይ ማልያ የለበሱ ሰዎች ይታያሉ። ሁለቱም ሜዳዎች ግን ልዩነቶች አሏቸው። አንደኛውን ሜዳ ደማቅ ቀለማማ የብርሃን ፍንጣቂ ከቦታል። አንደኛው ሜዳ ላይ ደግሞ ጨለማ ሠፍኗል። በሁለቱም ሜዳ ላይ ተመልካቾች አሉ። ባንደኛው ሜዳ ላይ ጢቅ ብለው የሞላው ሕዝብ ብርሃኑን መልሶ ያንጸባርቃል። በሌላኛው ሜዳ ላይ ደግሞ የተቸረከሙት ጥቂት ሰዎች በዘረኝነቱን ጨለማ ተውጠዋል። በሁለቱም ሜዳዎች ላይ ሰዎች ይታያሉ። ምነው ታድያ አንደኛው ሜዳ ላይ ያሉት ሰዎች እንደ ኃጢዓቱ ምርከኞች ኩርምት አሉ?
እነዚህን ወገኖች ነጻ ማውጣት አለብን። እነዚህን ወገኖች ከጨለማው አውጥተን ወደ ብርሃኑ ለማምጣት ማስተማር፣ መምከር አለብን። ታድያ እንዴት ይሆናል! እኔም ጭንቅ አለኝ!
አዎ - ይህን ሳሰላስል ድንገት ቶሮንቶ (Toronto) ላይ እምዬ ሚኒልክ ምስላቸው ብቅ አለ። በግርማ ሞገሥ የተከበቡት፣ የዋህና ደጉ ንጉሣችን እምዬ ሚኒልክ በፈረሳቸው ዳኛው ላይ ተቀምጠው ድንገት ብቅ ሲሉ ታየኝ። በስታድዮሙ ውስጥ ሌላ ብርሃን ተንጸባረቀ። በምድረ ዓለም ገድላቸው ተነግሮ ያላበቃው የነጻነቱ አባት እምዬ ሚኒልክ "ይህችን ባንዲራ ጠብቋት፣ ብዙዎች ለዚህች ባንዲራ ሲሉ ተሰውተዋል" አሉ በዚያ የዋህ ድምጻቸው። ይህ ድምጽ የስታድዮሙን ግድግዳና የአካባቢውን ሕንጻ በርቅሶ፣ በአየር እየተንሳፈፈ አኤስዋኖች (AESA One)ኩርምት ብለው የቀመጡበት አሌክሳንዴርያ ቨርጂንያ (Alexandria, Virginia)ጨለማው ዋሻ ደረሰ። ድምጹ እንደ ሳይክሎኑ( cyclone) ነፋስ ገረፋቸው፣ ገፈታተራቸው። አዎ እነዚህ በነዋይ ምርኮ ታግደው፣ ቀለብ ተሰፍሮላቸው በጨለማው ውስጥ ዘረኝነቱን ለማድመቅ የተቀመጡ የዋሆች በቶሎ ነጻ ይወጣሉ። የእምዬ ሚኒልክ ድምጽ እንኳንስ ለወገን ለባዕድም ማዕዛ አለው። ነዋይና ስጋቸው በእሳት እንደተበየደ ብረቶች ከተዋሃደው ጥቂቶቹ ቱባ የዘረኝነቱ አዳማቂዎች በቀር ሌሎቹ ቶሎ ነጻ ይወጣሉ።
አሁንም ጭንቅ ይለኛል። በደጉ ዘመን ተንቀባረው ይኖሩ የነበሩት፣ በዘመኑ አጠራር "የዲታ ልጆች" የሚባሉት ግለሰቦች ለምን ለጨለማው ሥራ ተባባሪዎች እንደሆኑ ማወቅ አልቻልኩም። ወያኔ በአብዛናው በሥሩ ያሰለፋቸው ምርከኖች ትላንት "በአማራው ስትጨኮን የነበርህ ነህ" የተባሉ ጥቂት ተላላ ድንባዣሞች ሆኖ ሳለ - ያኔ ተንቀባረው ያደጉ ግለሰቦች ለምን ምርከኞች እንደሆኑ ማሰቡ ያዳግታል። ገንዘቡ አታሏቸው ነው እንዳይባል እኛ የሳር ፍራሽ ሲበዛብን እነሱ ተዝቆ የማያልቅ ገንዘብ ተንተርሰው ያደጉ ቅምጥሉች ናቸው። ሥልጣን ፈልገው ነው እንዳይባል ደግሞ ሥልጣን የያዙ አልያም የባለሥልጣኖች መጋቢ አሽከር ተከታይ ሆኑ እንጂ የነእገሌን ያህል እንኳን ክብር አልተሰጣቸውም። ምንድነው እነዚህን ግለሰቦች ለዘረኝነቱ ጨለማ ተገዥ ያደረጋቸው። ንዋይ፤ ሥልጣን፤ የተወረሰባቸውን ቦታና ቤት ለማስመለስ ወይንስ የዓዕምሮ መላሸቅ? ያ ሁሉ ትምህርት ምነው ላሸቀ እነዚህን ወገኖችም እንዴት አድርገን ነጻ እንደምናወጣ አላውቅም። አንድም ሰው ቢሆን በዘረኝነቱ ጨለማ በምርኮ እንዲሰቃይ አንፈልግም። ለነዚህም ወገኖች መልካም ልብ እንስጣቸው። በጓደኞቻቸው እናስመክራቸው።
ኤስዋን AESA One ሰዎች ከዚህ ውርደት ልትማሩ ይገባል። ሕዝብ በማይደግፈው ነገር ውስጥ ከመሳተፍ ልትቆጠቡ ይገባል። ዲሞክራሲ ማለት የአብዛኛ ሕዝብ የበላይነት ማለት ነው። ይህ ደግሞ ሳይገባችሁ አይቀርም። ቁጥሩን መገመት ትችላላችሁ። ዘረኝነት አናሳ ነው። ዘረኝነት ኢትዮጵያዊነት አይደለም። ኃያላኑ ሃገሮች ለጊዜዊው ጥቅማቸው ሲሉ ዘረኝነቱን ቢያሞካሹትም እንኳን እናንተ የእምዬ ሚኒልክ ልጆች ልትታለሉ አይገባም። ነገ እንትፍ ብለው ከሚጥሉት ዘረኝነት ጋር ብትወግኑ ነገ የምታዝኑት እናንተው ናችሁ። ለልጅ ልጆቻችሁ ነጻነት ከወዲሁ አስቡበት። የባንዳ ልጅ፤ የምንትስ ልጅ ለምንስ ይባሉ።
ኤስፍና ESFNA እና AESA One የዲያስፖራው ኢትዮጵያው ሌላኛው የግብግብ አውድማዎች ናቸው። ግብግቡ ሰው ከሰው ጋር አይደለም። ግብግቡ ኢትዮጵያዊነት ከዘረኝነት ጋር ነው። ከእግዚአብሄር መንፈስ ጋር አታመሳስሉት እንጂ ሁለቱም መንፈሶች ናቸው። አንዱ ኢትዮጵያዊ መንፈስ፣ አንዱ የዘረኝነቱ የጣር መንፈስ። የኋላ ኋላ የዘረንነቱ የጣር መንፈስ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መሸነፉ አይቀርም። ይህ እውን እስኪሆን ለጥቂት ጊዜ ግብግቡ ይቀጥላል።
እነዚህን ወገኖች ነጻ ማውጣት አለብን። እነዚህን ወገኖች ከጨለማው አውጥተን ወደ ብርሃኑ ለማምጣት ማስተማር፣ መምከር አለብን። ታድያ እንዴት ይሆናል! እኔም ጭንቅ አለኝ!
አዎ - ይህን ሳሰላስል ድንገት ቶሮንቶ (Toronto) ላይ እምዬ ሚኒልክ ምስላቸው ብቅ አለ። በግርማ ሞገሥ የተከበቡት፣ የዋህና ደጉ ንጉሣችን እምዬ ሚኒልክ በፈረሳቸው ዳኛው ላይ ተቀምጠው ድንገት ብቅ ሲሉ ታየኝ። በስታድዮሙ ውስጥ ሌላ ብርሃን ተንጸባረቀ። በምድረ ዓለም ገድላቸው ተነግሮ ያላበቃው የነጻነቱ አባት እምዬ ሚኒልክ "ይህችን ባንዲራ ጠብቋት፣ ብዙዎች ለዚህች ባንዲራ ሲሉ ተሰውተዋል" አሉ በዚያ የዋህ ድምጻቸው። ይህ ድምጽ የስታድዮሙን ግድግዳና የአካባቢውን ሕንጻ በርቅሶ፣ በአየር እየተንሳፈፈ አኤስዋኖች (AESA One)ኩርምት ብለው የቀመጡበት አሌክሳንዴርያ ቨርጂንያ (Alexandria, Virginia)ጨለማው ዋሻ ደረሰ። ድምጹ እንደ ሳይክሎኑ( cyclone) ነፋስ ገረፋቸው፣ ገፈታተራቸው። አዎ እነዚህ በነዋይ ምርኮ ታግደው፣ ቀለብ ተሰፍሮላቸው በጨለማው ውስጥ ዘረኝነቱን ለማድመቅ የተቀመጡ የዋሆች በቶሎ ነጻ ይወጣሉ። የእምዬ ሚኒልክ ድምጽ እንኳንስ ለወገን ለባዕድም ማዕዛ አለው። ነዋይና ስጋቸው በእሳት እንደተበየደ ብረቶች ከተዋሃደው ጥቂቶቹ ቱባ የዘረኝነቱ አዳማቂዎች በቀር ሌሎቹ ቶሎ ነጻ ይወጣሉ።
አሁንም ጭንቅ ይለኛል። በደጉ ዘመን ተንቀባረው ይኖሩ የነበሩት፣ በዘመኑ አጠራር "የዲታ ልጆች" የሚባሉት ግለሰቦች ለምን ለጨለማው ሥራ ተባባሪዎች እንደሆኑ ማወቅ አልቻልኩም። ወያኔ በአብዛናው በሥሩ ያሰለፋቸው ምርከኖች ትላንት "በአማራው ስትጨኮን የነበርህ ነህ" የተባሉ ጥቂት ተላላ ድንባዣሞች ሆኖ ሳለ - ያኔ ተንቀባረው ያደጉ ግለሰቦች ለምን ምርከኞች እንደሆኑ ማሰቡ ያዳግታል። ገንዘቡ አታሏቸው ነው እንዳይባል እኛ የሳር ፍራሽ ሲበዛብን እነሱ ተዝቆ የማያልቅ ገንዘብ ተንተርሰው ያደጉ ቅምጥሉች ናቸው። ሥልጣን ፈልገው ነው እንዳይባል ደግሞ ሥልጣን የያዙ አልያም የባለሥልጣኖች መጋቢ አሽከር ተከታይ ሆኑ እንጂ የነእገሌን ያህል እንኳን ክብር አልተሰጣቸውም። ምንድነው እነዚህን ግለሰቦች ለዘረኝነቱ ጨለማ ተገዥ ያደረጋቸው። ንዋይ፤ ሥልጣን፤ የተወረሰባቸውን ቦታና ቤት ለማስመለስ ወይንስ የዓዕምሮ መላሸቅ? ያ ሁሉ ትምህርት ምነው ላሸቀ እነዚህን ወገኖችም እንዴት አድርገን ነጻ እንደምናወጣ አላውቅም። አንድም ሰው ቢሆን በዘረኝነቱ ጨለማ በምርኮ እንዲሰቃይ አንፈልግም። ለነዚህም ወገኖች መልካም ልብ እንስጣቸው። በጓደኞቻቸው እናስመክራቸው።
ኤስዋን AESA One ሰዎች ከዚህ ውርደት ልትማሩ ይገባል። ሕዝብ በማይደግፈው ነገር ውስጥ ከመሳተፍ ልትቆጠቡ ይገባል። ዲሞክራሲ ማለት የአብዛኛ ሕዝብ የበላይነት ማለት ነው። ይህ ደግሞ ሳይገባችሁ አይቀርም። ቁጥሩን መገመት ትችላላችሁ። ዘረኝነት አናሳ ነው። ዘረኝነት ኢትዮጵያዊነት አይደለም። ኃያላኑ ሃገሮች ለጊዜዊው ጥቅማቸው ሲሉ ዘረኝነቱን ቢያሞካሹትም እንኳን እናንተ የእምዬ ሚኒልክ ልጆች ልትታለሉ አይገባም። ነገ እንትፍ ብለው ከሚጥሉት ዘረኝነት ጋር ብትወግኑ ነገ የምታዝኑት እናንተው ናችሁ። ለልጅ ልጆቻችሁ ነጻነት ከወዲሁ አስቡበት። የባንዳ ልጅ፤ የምንትስ ልጅ ለምንስ ይባሉ።
ኤስፍና ESFNA እና AESA One የዲያስፖራው ኢትዮጵያው ሌላኛው የግብግብ አውድማዎች ናቸው። ግብግቡ ሰው ከሰው ጋር አይደለም። ግብግቡ ኢትዮጵያዊነት ከዘረኝነት ጋር ነው። ከእግዚአብሄር መንፈስ ጋር አታመሳስሉት እንጂ ሁለቱም መንፈሶች ናቸው። አንዱ ኢትዮጵያዊ መንፈስ፣ አንዱ የዘረኝነቱ የጣር መንፈስ። የኋላ ኋላ የዘረንነቱ የጣር መንፈስ በኢትዮጵያዊነት መንፈስ መሸነፉ አይቀርም። ይህ እውን እስኪሆን ለጥቂት ጊዜ ግብግቡ ይቀጥላል።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር፣ ባዲራችን ለዘላለም ትውለብለብ።
ክብር ለአጼ ቴዎድሮስ፣ ክብር ለአጼ ዮሃንስ፣ ክብር ለእምዬ ሚኒልክ
ክብር ለአጼ ቴዎድሮስ፣ ክብር ለአጼ ዮሃንስ፣ ክብር ለእምዬ ሚኒልክ
Saturday, April 2, 2016
በ ወያኔ ዘመን................
በ ወያኔ ዘመን................
ባጠቅላይ ሃቀኝነት፣ ደግነት፣ ፍትሃዊነት፣ ሙስናንና ጉቦን መጸየፍ – እነዚህ የሕዝቡ የመልካም ባህርይ መገለጫ የሆኑት እሴቶች በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ጉሮኖ ተወርውረዋል። እነዚህን እሴቶች ዳግም ሊያንጸባርቅ የሞከረ ሁሉ መሳለቅያ ይሆናል። ኬንያና ናይጄርያ በሙስናና ጉቦ ጫፍ ላይ የደረሱ ሃገሮች እየተባሉ ሲነገር ቆይቷል። ኢትዮጵያ ደግሞ በጥቂት ዓመታት ክብረወሰኑን አልፋ የሙስናና ጉቦ ፍልስፍና የተሃድሶ ምድር እንደሆነች ይታወቃል። ይህን የመሳሰሉት ግፎች ናቸው ዛሬ ሕዝቡን ለአመጽ ያነሳሱት። የፍጥ መዛባት፣ እስር፣ ግድያና የምጣኔ ኃብቱ ይዞታ ልዩነት ካልተገደቡ በቀር ሕዝቡን ለመብቱ ከመታገል የሚያቆመው አንዳች ኃይል የለም። የፌደራል መንግሥቱ እጆች አመድ አፋሽዕ ወይም የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ እንዳሉትየኢትዮጵያ ሕዝብ ወርቅ ቢያነጥፉለትሆኖ አይደለም ይህ ሁሉ አመጽ የበረከተው። ሙስናው፣ የአስተዳደር በደሉ ፡ ኑሮውን አናግተውበት ፡ በድህነትና ሰቆቃ ጅራፍ መገረፉ፣ በአምባገነኖች ውሳኔ ብቻ መነዳቱ አልበቃ ብሎ ቀማኞች መሬቱንና የመሬቱን የተፈጥሮ ገጸበረከት በጠመንጃ አስገድደው በጠራራ ፀሃይ ስለሚዘርፉት እንጂ።እግዚአብሄር ቸር ዘመን ያምጣልን፣ አሜን

ባጠቅላይ ሃቀኝነት፣ ደግነት፣ ፍትሃዊነት፣ ሙስናንና ጉቦን መጸየፍ – እነዚህ የሕዝቡ የመልካም ባህርይ መገለጫ የሆኑት እሴቶች በኢትዮጵያ ውስጥ ወደ ጉሮኖ ተወርውረዋል። እነዚህን እሴቶች ዳግም ሊያንጸባርቅ የሞከረ ሁሉ መሳለቅያ ይሆናል። ኬንያና ናይጄርያ በሙስናና ጉቦ ጫፍ ላይ የደረሱ ሃገሮች እየተባሉ ሲነገር ቆይቷል። ኢትዮጵያ ደግሞ በጥቂት ዓመታት ክብረወሰኑን አልፋ የሙስናና ጉቦ ፍልስፍና የተሃድሶ ምድር እንደሆነች ይታወቃል። ይህን የመሳሰሉት ግፎች ናቸው ዛሬ ሕዝቡን ለአመጽ ያነሳሱት። የፍጥ መዛባት፣ እስር፣ ግድያና የምጣኔ ኃብቱ ይዞታ ልዩነት ካልተገደቡ በቀር ሕዝቡን ለመብቱ ከመታገል የሚያቆመው አንዳች ኃይል የለም። የፌደራል መንግሥቱ እጆች አመድ አፋሽዕ ወይም የቀድሞው የኢትዮጵያ መሪ ኮሎኔል መንግሥቱ እንዳሉትየኢትዮጵያ ሕዝብ ወርቅ ቢያነጥፉለትሆኖ አይደለም ይህ ሁሉ አመጽ የበረከተው። ሙስናው፣ የአስተዳደር በደሉ ፡ ኑሮውን አናግተውበት ፡ በድህነትና ሰቆቃ ጅራፍ መገረፉ፣ በአምባገነኖች ውሳኔ ብቻ መነዳቱ አልበቃ ብሎ ቀማኞች መሬቱንና የመሬቱን የተፈጥሮ ገጸበረከት በጠመንጃ አስገድደው በጠራራ ፀሃይ ስለሚዘርፉት እንጂ።እግዚአብሄር ቸር ዘመን ያምጣልን፣ አሜን

Saturday, March 26, 2016
ፍትህ በ ወያኔ ዘመን
ፍትህ (justice)፣ በኢትዮጵያ ፍትህ ደብዝዛለች። ደብዳቢውና ተደብዳቢው ፖሊስ ጣብያ ቢሄዱ ተደብዳቢው ይታሠራል። ዘራፊና ተዘራፊ ሸንጎ ፊት ቢቀርቡ ተዘራፊው ተሸማቆ ከእልፍኙ በአፋጣኝ እንዲወጣ ይደረጋል። ዳኛና ጠበቃ የጥቅም ትሥሥር አድርገዋል። ፍርደ ገምድል ዳኛው የባለጉዳዩን ሳይሆን የጠበቃውን እጆች ያያል። ደህና ጉቦ ሰጪ ጠበቃ ዝናን ያተርፋል፣ በርካታ ደንበኞች ያፈራል። ለፍትህ የቆሙ ጠበቆች ደግሞ ሥራ ፈተዋል። "ፍትህ ይስፈን" እያሉ ሲጮኹ ሙሰኛው ዳኛና መሠሪው ጠበቃ ይሳለቁባቸዋል። ፍትህ በኢትዮጵያ እጅግ ተረግጣለች። ታድያ በአቋራጭ ለመክበር ኢፍትሃዊ ነገሮችን ሳይፈሩ መፈጸም እየተለመደ መጥቷል። በኢፍትሃዊ አሠራሮች ልምድን የቀሰሙት ደላሎችና አቀባባዮች የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ። እነርሱ ለዳኞችና ጠበቆች ሐሰትን አደልቦ እንደምን ማሸነፍ እንደሚቻል ህግን ሳይፈሩ፣ ሰውን ሳያፍሩ ምክር ያካፍሏሉ። ክፉዎች የምክር አገልግሎት በሚሰጡባቸው ቢሯቸው ውስጥ የፍትሃብሄር ህግና መጽሃፍ ቅዱስ ሁለቱም ጠረቤዛው ላይ ተቀምጠዋል። አይ ዘመን!


ፍትህ (justice)፣ በኢትዮጵያ ፍትህ ደብዝዛለች። ደብዳቢውና ተደብዳቢው ፖሊስ ጣብያ ቢሄዱ ተደብዳቢው ይታሠራል። ዘራፊና ተዘራፊ ሸንጎ ፊት ቢቀርቡ ተዘራፊው ተሸማቆ ከእልፍኙ በአፋጣኝ እንዲወጣ ይደረጋል። ዳኛና ጠበቃ የጥቅም ትሥሥር አድርገዋል። ፍርደ ገምድል ዳኛው የባለጉዳዩን ሳይሆን የጠበቃውን እጆች ያያል። ደህና ጉቦ ሰጪ ጠበቃ ዝናን ያተርፋል፣ በርካታ ደንበኞች ያፈራል። ለፍትህ የቆሙ ጠበቆች ደግሞ ሥራ ፈተዋል። "ፍትህ ይስፈን" እያሉ ሲጮኹ ሙሰኛው ዳኛና መሠሪው ጠበቃ ይሳለቁባቸዋል። ፍትህ በኢትዮጵያ እጅግ ተረግጣለች። ታድያ በአቋራጭ ለመክበር ኢፍትሃዊ ነገሮችን ሳይፈሩ መፈጸም እየተለመደ መጥቷል። በኢፍትሃዊ አሠራሮች ልምድን የቀሰሙት ደላሎችና አቀባባዮች የምክር አገልግሎት ይሰጣሉ። እነርሱ ለዳኞችና ጠበቆች ሐሰትን አደልቦ እንደምን ማሸነፍ እንደሚቻል ህግን ሳይፈሩ፣ ሰውን ሳያፍሩ ምክር ያካፍሏሉ። ክፉዎች የምክር አገልግሎት በሚሰጡባቸው ቢሯቸው ውስጥ የፍትሃብሄር ህግና መጽሃፍ ቅዱስ ሁለቱም ጠረቤዛው ላይ ተቀምጠዋል። አይ ዘመን!


Subscribe to:
Posts (Atom)

